Popular Posts

Tuesday, April 3, 2018

ስንፈጠር ምን ነበርን?

ስለ አንድ ነገር ትክክለኛውን ነገር ለመረዳት ካስቸገረ ስለዚያ ነገር ለመረዳት ወደ ቀድሞው ነገሩ መመለስ በጣም ወሳኝ ነው፡፡ ስለአንድ ነገር ክርክር ከተነሳ ቀድሞ ምን እንደነበረ ማወቅ ለክርክሩ መቋጫ ያደርግለታል፡፡
ደቀመዛሙርቱ በጊዜ ሂደት ውስጥ ስለተለወጠው የትዳር ህግ ኢየሱስን ሲጠይቁት የመለሰላቸው መልስ ይህ ነበር፡፡ አዎ የምትሉት እውነት ነው፡፡ ነገር ግን ከመጀመሪያ እንደዚህ አልበነረም፡፡
የእግዚአብሄርን የመጀመሪያውን ሃሳብ ለመረዳት ወደ መጀመሪያ ታሪኩ መመለስ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡
እነርሱም፦ እንኪያስ ሙሴ የፍችዋን ጽሕፈት ሰጥተው እንዲፈቱአት ስለ ምን አዘዘ? አሉት። እርሱም፦ ሙሴስ ስለ ልባችሁ ጥንካሬ ሚስቶቻችሁን ትፈቱ ዘንድ ፈቀደላችሁ፤ ከጥንት ግን እንዲህ አልነበረም። ማቴዎስ 19፡7-8
በየጊዜው ስለሰው ማንነት የተለያ አወዛጋቢ ትንታኔዎች ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡ አሁንም ሰው ከየት እንደመጣና ወደፊት ምን እንደሚሆን የተለያዩ መላምቶች ይሰጣሉ፡፡ ስለሰው ማንነት ለማወቅ በመጀመሪያ የነበረውን ታሪክ መመልከት እውነተኛውን እውቀት ይሰጠናል፡፡
ሰው እንዴት እንደተፈጠረ መመልከት ሰው ከየት እንደመጣ ማን እንደሆነ እውቀትን ያስጨብጠናል፡፡
እግዚአብሄር ሰውን በድንገት አልፈጠረውም፡፡ እግዚአብሄር በድንገት ሰው የሚባለ ፍጥረት አላገኘም፡፡ እግዚአብሄር ሰውን ከመፍጠሩ በፊት ምን አይነት ፍጥረት መፍጠር እንደሚፈልግ አስቦበት ነበር፡፡ እግዚአብሄር ፍጥረቱን ከመፍጠሩ በፊት ይህ ፍጥረት ምንን መስሎ እንደሚፈጠር ፣ በምን ሁኔታ እንደሚፈጠር ፣ ምን እንደሚያደርግለት ሁሉንም ነገር አስቀድሞ አቅዶና አስቦበት ነው ሰውን የፈጠረው፡፡
እግዚአብሔርም አለ፦ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ። ዘፍጥረት 1፡26
ሰው ሲፈጠር እግዚአብሄር ያየውን ነገር እንዲሰራ ለዚያው ለተፈጠረበት አላማ ዲዛይን ተደርጎ ነው የተፈጠረው፡፡
እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው። ዘፍጥረት 1፡26-27
እግዚአብሄር ሰውን እንዴት እንደ ፈጠረው ከቃሉ በመረዳት ሰው ከየት እንደመጣና ወደየት እንደሚሄድ መረዳትን ማግኘት እንችላለን፡፡
እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፤ በአፍንጫውም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት ሰውም ሕያው ነፍስ ያለው ሆነ። ዘፍጥረት 1፡7
እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው በምድር ላየ እንበዲኖር በመሆኑ ለምድር የሚስማማ ቤትን ፈጠረለት፡፡ እግዚአብሄ ሰውን የላከው በምድር ላይ በመሆኑ ለምድር ኑሮ የሚስማማ መኖሪያን ከምድር አዘጋጀለት፡፡ እግዚአብሄር የሰውን መኖሪያ ቤት የሰውን ስጋ ከምድር አፈር አበጀው፡፡ እግዚአብሄር ከምድር አፈር ያበጀው የሰው በምድር ላይ መኖሪያ ቤት ነው፡፡
እግዚአብሄር ከምድር ያዘጋጀው የሰው መኖሪያ ቤት ሰው ዝንደሌለበት ቤት ባዶ ነበር፡፡ እግዚአብሄ ከምደር አፈር ያበጀው የሰው ስጋ በሰው እንዳልተለበሰ ልብስ ባዶ እና የሞተ ነበር፡፡
እግዚአብሄር የፈጠረው የሰው ስጋ ስሜት ያለው ፈቃድ ያለው ሃሳብ ያለው አልነበረም፡፡ እግዚአብሄር ያበጀው የሰው ስጋ ሙት ነበር፡፡ ሰው ስጋ ስላይደለ እግዚአብሄር ያበጀው የሰው ስጋ የምድር አካል የሆነ አፈር ብቻ ነበር፡፡ ስጋ በእግዚአብሄር መልክና አምሳል አልተፈጠረም፡፡ ስጋ በእግዚአብሄር መልክና አምሳሉ የተፈጠረ የሰው መኖሪያ እንጂ ሰው አይደለም፡፡
ከምድር አፈር የተበጀውን የሰው ስጋ እንዲሆን ያደረገው እግዚአብሄር በመልኩና በአምሳሉ የፈጠረው ሰው ነው፡፡  
እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፤ በአፍንጫውም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት ሰውም ሕያው ነፍስ ያለው ሆነ። ዘፍጥረት 1፡7
እግዚአብሄር የህይወትን እስትንፋስ እፍ እስካለበት ጊዜ ድረስ ከምድር የተበጀው ቢያነሱት ተመልሶ የሚወድቅ ፣ ቢያቆሙት የማይቆም ፣ ስሜት የሌለው ፣ ሃሳብ የሌለውና ፈቃድ የሌለው ሬሳ ብቻ ነበር፡፡
የህይወት እስትንፋስ እፍ ካለበት በኋላ ብቻ ነበር ሰው ህያው ነፍስ ሆነ ተብሎ የተፃፈው፡፡
ሰው የተገኘው ከእግዚአብሄር ነው፡፡ ስጋው ወደነበረበት ምድር ይመለሳል፡፡ ሰው ግን ወደሰጠው ወደ እግዚአብሄር ይመለሳል፡፡ 7
አፈርም ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ፥ ነፍስም ወደ ሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ። መክብብ 12፡7
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #በክርስቶስ #መንፈስ #ማንነት #መልክ #አምሳል #የእግዚአብሄርልጅ #ክብር  #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ማየት #አፈር #ስጋ #ቤት #የእግዚአብሄርመንግስት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አዲስፍጥረት #ክርስቶስ #የእግዚአብሄርቤተሰብ

No comments:

Post a Comment