Popular Posts

Saturday, April 21, 2018

ተአምራት ነን

እነሆ፥ እኔና እግዚአብሔር የሰጠኝ ልጆች ለእስራኤል በጽዮን ተራራ ከሚኖረው ከሠራዊት ጌታ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምልክትና ተአምራት ነን። ኢሳያስ 8፡18
ለእግዚአብሄር ክብር ተፈጥረናል፡፡ የእግዚአብሄር ልጆች ነን፡፡ በምድር ላይ እግዚአብሄርን እንወክላለን፡፡ የእግዚአብሄርን ፈቃድ በምድር ላይ እናስፈጽማለን፡፡
ስምህ ይቀደስ፤ መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፤ ማቴዎስ 6፡10
ኑሮዋችን በእምነት ነው፡፡ እግዚአብሄር ከእኛ ጋር ነው፡፡
እግዚአብሄር ይረዳናል፡፡
ይሹሩን ሆይ፥ በሰማያት ላይ ለረድኤትህ፥ በደመናትም ላይ በታላቅነት እንደሚሄድ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማንም የለም። ዘዳግም 33፡26
የእግዚአብሄር ልጆች ነን፡፡ ከምድር አይደለንም፡፡ በምድር ላይ በእግዚአብሄር ልጅነት ስልጣን እንኖራለን፡፡  
ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ ዮሃንስ 1፡12
ሃይማኖት ሃይማኖት ጫወታ እየተጫወትን አይደለም፡፡ ኢየሱስ በልባችን ይኖራል፡፡ ብቃታችን ኢየሱስ ራሱ ነው፡፡ የምንኖረው በእርሱ ነው፡፡
በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ፤ ወይስ ምናልባት የማትበቁ ባትሆኑ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ እንዳለ ስለ እናንተ አታውቁምን? 2ኛ ቆሮንቶስ 13፡5
በምድር ላይ በእግዚአብሄር ሃይል እንኖራለን፡፡ በምድር ላይ በእግዚአብሄር ስልጣን እንኖራለን፡፡
ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፦ ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ። እንግዲህ ሂዱና . . . እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ። ማቴዎስ 28፡18-20
ለምድር ሰዎች እንግዳ ነን፡፡ ለምድር ሰዎች እግዚአብሄር እንደሚሰራ ምልክቶች ነን፡፡ ለምድር ሰዎች ድንቅና ተአምራት ነን፡፡
ሕዝቡም አይተው ተደነቁ፥ ለሰውም እንዲህ ያለ ሥልጣን የሰጠ እግዚአብሔርን አከበሩ። ማቴዎስ 9፡8
እነሆ፥ እኔና እግዚአብሔር የሰጠኝ ልጆች ለእስራኤል በጽዮን ተራራ ከሚኖረው ከሠራዊት ጌታ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምልክትና ተአምራት ነን። ኢሳያስ 8፡18
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪ #ፀጋ #ተአምር #የሚያስችልሃይል #ድንቅ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #የእግዚአብሄርችሎታ #እግዚአብሄርንሃያል #ራስንመግዛት #ልብ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment