Popular Posts

Friday, April 20, 2018

መስቀልን መሸከም

ኢየሱስ በማያወላዳ ሁኔታ ሊከተሉት የሚወዱ ሁሉ መስቀላቸውን ተሸክመው እንዲከተሉት አስተምሮዋል፡፡ ይህም ብቻ አይደለም መስቀሉን ተሸክሞ የማይከተለው ሰው ለእርሱ ሊሆን እንደመይገባው በግልፅ ተናግሮዋል፡፡
የደቀመዝሙርነት መመዘኛው የራሰን መስቀል ተሸክሞ ጌታን መከተል ነው፡፡
ማንም መስቀሉን ተሸክሞ በኋላዬ የማይመጣ፥ ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም። ሉቃስ 14፡27
ኢየሱስን ለመከረተል ራስን መካድ ያስፈልጋል፡፡ ኢየሱስን ጌታ ለማድርግ ከራስ ጌትነት መውረድ ያስፈልጋል፡፡ ጌታንም ነፍሳችንም ማስደሰት አንችልም፡፡ ራሱን የካደ ሰው ብቻ ነው መስቀሉን ተሸክሞ ሊከተል የሚችለው፡፡
በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አለ፦ እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ። ማቴዎስ 16፡24
መስቀል ግን ምንድነው ብለን መረዳት እየሱስ ያዘዘን ትእዛዝ በሚገባ ፈፅመን ጌታን እንዳከብረው ይረዳናል፡፡ እንድንሸከመው የታዘዝነው መስቀል በእንጨት የተሰራ ግኡዝ ነገር እንዳይደለ እናውቃለን፡፡
መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም። ማቴዎስ 10፡38
መስቀል እንደእግዚአብሄር ቃል የመኖር ሃላፊነት ነው፡፡ መስቀልን መሸከም ከእግዚአብሄር ቃል ውጭ ላለመኖር የመወሰን ሃላፊነት ነው፡፡ መስቀል እግዚአብሄር በህይወታችን ያስቀመጠውን ሃላፊነትን እንጂ የፈለግነውን ነገር ያለማድረግ ሃላፊነት ነው፡፡ መስቀልን መሸከም ራስን የመካድ ሃላፊነት ነው፡፡ መስቀልን መሸከም የሚመቸንን ነገር ሳይሆን ጌታ ያዘዘንን ነገር ለማድረግ መጨከን ነው፡፡ መስቀልን መሸከም የተሻለን ነገር ሳይሆን የእግዚአብሄርን ነገር ለማድረግ መቁረጥ ነው፡፡ መስቀልን መሸከም የእግዚአብሄርን ነገር ለማድረግ የሚመጣብንን ማንኛውንም መከራ መቀበል ነው፡፡ በአጠቃላይ አነጋገር መስቀል የህይወት ሃላፊነት ነው፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #መስቀል #ስቅለት #ሃላፊነት #ውሳኔ #መጨከን #መከራ #ፈተና #መካድ #ደቀመዝሙር #ጌታ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ተፈፀመ #ቤተመቅደስ #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment