Popular Posts

Saturday, March 31, 2018

ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም

ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም። ዮሐንስ 1513
ገና ደካሞች ሳለን ክርስቶስ ዘመኑ ሲደርስ ስለ ኃጢአተኞች ሞቶአልና። ስለ ጻድቅ የሚሞት በጭንቅ ይገኛልና፤ ስለ ቸር ሰው ግን ሊሞት እንኳ የሚደፍር ምናልባት ይገኝ ይሆናል። ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል። ሮሜ 5፡6-8
ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥ ኤፌሶን 2፡4-5
ስለዚህ ከዚህ በላይ የሚቀርብ መስዋእት የለም፡፡
የእነዚህም ስርየት ባለበት ዘንድ፥ ከዚህ ወዲህ ስለ ኃጢአት ማቅረብ የለም። ዕብራውያን 10፡18
ስለሃጢያታችን አንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መስዋትን አድርጎዋል፡፡
እርሱም እንደነዚያ ሊቃነ ካህናት አስቀድሞ ስለ ራሱ ኃጢአት በኋላም ስለ ሕዝቡ ኃጢአት ዕለት ዕለት መሥዋዕትን ሊያቀርብ አያስፈልገውም፤ ራሱን ባቀረበ ጊዜ ይህን አንድ ጊዜ ፈጽሞ አድርጎአልና። ዕብራውያን 7፡27
ይህንን ታላቅ መዳን መዳን ቸል ብንለው፥ አናመልጥም፡፡
በመላእክት የተነገረው ቃል ጽኑ ከሆነ፥ መተላለፍና አለመታዘዝም ሁሉ የጽድቅን ብድራት ከተቀበለ፥ እኛስ እንዲህ ያለውን ታላቅ መዳን ቸል ብንለው፥ እንዴት እናመልጣለን? ዕብራውያን 2፡2
ይህንን እውቀት ካወቅን በኋላ ወደን ሃጢያት ብናደርግ ከዚህ በኋላ የሃጢያተ መስዋእት አይኖርም፡፡
የእውነትን እውቀት ከተቀበልን በኋላ ወደን ኃጢአት ብናደርግ ከእንግዲህ ወዲህ ስለ ኃጢአት መሥዋዕት አይቀርልንምና፥ ዕብራውያን 10፡26
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ፋሲካ #ትንሳኤ #ስቅለት #በዓል #መስዋእት #ቤዛነት #መቤዠት #የሚበልጥ #ፍቅር #ተስፋ #ደስታ #መስዋእት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ብርሃን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  #የዋህነት #ንፁህ

በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም

በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ 1ኛ ቆሮንቶስ 6፡19-20
በሰው ህይወት የባለቤትነት ጥያቄ ሲመለስ ብዙ ጥያቄዎች ይመለሳሉ፡፡ የባለቤትነት ጥያቄ ሲመለስ የተለያዩ የመብት ጥያቄዎች  ይመለሳሉ፡፡
አንድ ነገር የማን ነው የሚለው ጥያቄ ሲመለስ ማን መብት አለው የሚለውም ጠያቄ አብሮ ይመለሳል፡፡ አንድ ነገር ባለቤቱ ማን አንደሆነ ጥርት ያለ ነገር ከሌለ በነገሩ ላይ ማን ምን መብት አለው የሚለው ጥያቄ ሊመለስ አይችልም፡፡
እግዚአብሄር እኛን የፈጠረን ለክብሩ ነው፡፡ እግዚአብሄር እኛን የፈጠረን ለራሱ ነው፡፡ እግዚአብሄር የፈጠረን ለእኛ ለራሳችን አይደለም፡፡ ይህን እውነት ካልተረዳን ሌላ ምንም እውነት ልንረዳ አንችልም፡፡ በዚህ ካልተግባባን በሌላ በምንም ልንግባባ አንችልም፡፡ እኛ ፈጣሪዎች አይደለንም፡፡ እኛ የእግዚአብሄር የፈጠረን ፍጡሮች ነን፡፡ የህይወታችን ባለቤት እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
እርሱ አምላካችን ነውና፥ እኛ የማሰማርያው ሕዝብ የእጁም በጎች ነንና። መዝሙር 95፡7
እግዚአብሄር ለክብሩ ፈጥሮናል፡፡ እኛ የእርሱ ነን፡፡ እኛ የራሳችን አይደለንም፡፡
በስሜ የተጠራውን ለክብሬም የፈጠርሁትን፥ የሠራሁትንና ያደረግሁትን ሁሉ አምጣ እለዋለሁ። ኢሳያስ 43፡6-7
እግዚአብሄር በእኛ ላይ ሙሉ ባለመብት ነው፡፡ እኛ በራሳችን ላይ መብት የለንም፡፡
እንደ ሸክላ ሠሪ ጭቃ የምትቈጠሩ አይደላችሁምን? በውኑ ሥራ ሠሪውን፦ አልሠራኸኝም ይለዋልን? ወይስ የተደረገው አድራጊውን፦ አታስተውልም ይለዋልን? ኢሳያስ 29፡16
ከሠሪው ጋር ለሚታገል ወዮለት! በምድር ሸክላዎች መካከል ያለ ሸክላ ነው። ጭቃ ሠሪውን፦ ምን ትሠራለህ? ወይስ ሥራህ፦ እጅ የለውም ይላልን? ኢሳያስ 459
ሰው እግዚአብሄር አታድርግ ያለውን ነገር በማድረግ በማመፁ ለሃጢያትና ለሰይጣን ተሽጦ ነበር፡፡ እግዚአብሄር ልጁን ኢየሱስን በመስቀል ላይ መስዋእት እንዲሆንልን በማድረግ እኛን በደሙ መልሶ ገዛን፡፡
በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት። ኤፌሶን 1፡7
አሁን ደግሞ በክርስቶስ ኢየሱስ አዳኝነት ያመንን ሁላችን  በክርስቶስ ኢየሱስ ደም በከበረ ዋጋ ተገዝተናል፡፡
ከአባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከከንቱ ኑሮአችሁ በሚያልፍ ነገር በብር ወይም በወርቅ ሳይሆን፥ ነውርና እድፍ እንደ ሌለው እንደ በግ ደም በክቡር የክርስቶስ ደም እንደ ተዋጃችሁ ታውቃላችሁ። 1ኛ ጴጥሮስ 1፡18-19
በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ 1ኛ ቆሮንቶስ 6፡19-20
ከአሁን በኋላ ለራሳችን በመሞት ህይወት ለሰጠን ለእርሱ እንኖራለን፡፡
ስለዚህ የራሳችን አይደለንም፡፡ ኢየሱስ የሞተው ለራሳችን እንድንሞት ነው፡፡ ኢየሱስ የሞተው ለሞተልን ለእርሱ እንድንኖር ነው እንጂ ወደፊት ለራሳችን እንዳንኖር ነው፡፡
ይህን ስለቆረጥን የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናልና፤ አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ፤ እንግዲያስ ሁሉ ሞቱ፤ በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ። 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡14-15
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ባለቤት #ዋጋ #መዋጀት #ብር #ወርቅ #ደም #ክብር #ራእይ #አላማ #ግብ #ውሳኔ #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ብርሃን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መንገድ #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

Friday, March 30, 2018

ከመስቀል ወርደህ ራስህን አድን

አንተስ የአሁድ ንጉሥ ከሆንህ፥ ራስህን አድን እያሉ ይዘብቱበት ነበር። ሉቃስ 23፡37
የሚያልፉትም ራሳቸውን እየነቀነቁ ይሰድቡት ነበርና። ዋ፥ ቤተ መቅደስን የምታፈርስ በሦስት ቀንም የምትሠራ፥ ከመስቀል ወርደህ ራስህን አድን አሉ። ማርቆስ 15፡29-30
ኢየሱስ ለሃጢያታችን ሊሞት ወደ ምድር ሲመጣ የእኛን ስጋ ለብሶ ነው፡፡ ኢየሱስ በምድር ላይ ሲመላለስ በሁሉ ነገር እንደኛ ተፈትኖዋል፡፡
ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሲሰቀል ከመስቀል እንዲወርድና ሃይሉን እንዲያሳይ ተፈትኖዋል፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ ሃይሉን ከማሳየት ይልቅ ባሀሪን ማሳየት መረጠ፡፡ ኢየሱስ ሃይሉን ከማሳየት ይልቅ ሃይሉን ላለማሳየት መረጠ፡፡ ኢየሱስ ሃይሉን ለማሳየት ከመስቀል ከመውረድ ይልቅ በመስቀል በመቆየት በትግስት ደህንነታችንን መፈፀም መረጠ፡፡ ኢየሱስ ሃይሉን ከማሳየት ይልቅ እንደደካማ ተቆጠረ፡፡
ኢየሰስ ሃይሉን በማሳየትከሚገኝ እርካታ ይልቅ ሃይሉን ላለማሳየት ትህትናን መረጠ፡፡ ኢየሱስ ሃይሉን በማሳየት ዝነኛ ከመሆን ይልቅ በመስቀል የመሞትን ነውርን መረጠ፡፡ ኢየሱስ ነውርን አክብሮ በመስቀል ላይ ላለመሰቀል ሃይሉን ከማሳየት ይልቅ በመስቀል የመሞትን ነውርን ንቆ በመስቀል ላይ ለመሞት ታገሰ፡፡ ኢየሱስ ራሱን ለማዳን ሳይሆን ሰውን ለማዳን ነው ወደ ምድር የመጣው፡፡ ኢየሱስ ለራሱ ክብር ሳይሆን ሰውን ሊያከብር ነው በመስቀል ላይ የተዋረደው፡፡   
የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና። ዕብራውያን 12፡1-2
አሁንም እኛን ለአለም ሞተናል ተሰቅለናል ብለን ኢየሱስን የምንከተል ሁላችን ከመስቀል ውረድ እና ሃይልህን አሳየን የሚሉ ብዙ ነገሮች በህይወታችን ያጋጠሙናል፡፡ ስጋችን ፍቀድልኝ አንዴ ሃይሌን ላሳያቸው ይለናል፡፡  
እኛ ግን ሃይላችንን ከማሳየት ይልቅ የእግዚአብሄርን አላማ በህይወታችን ለመፈፀም መዋረድን እንመርጣለን፡፡ እኛ ሃይላችንን ከማሳየት ይልቅ ለእግዚአብሄር ሃሳብ መሸነፍን እንመርጣለን፡፡ ሃይላችንን አሳይተን በሰው ፊት ጎሽ ከመባል ይልቅ ሃይላችንን ላለማሳየት በመታገስ በእግዚአብሄር ፊት ብቻ ጎሽ መባልን እንመርጣለን፡፡  
ሁልጊዜ ከመስቀል ወረድ የሚለውን የፉክክር ጥሪ እንቢ ባልን መጠን እንደ ስንዴ ቅንጣት ተዘርተን ሞተን ብዙ ፍሬ ማፍራት እንችላለን፡፡
እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የስንዴ ቅንጣት በምድር ወድቃ ካልሞተች ብቻዋን ትቀራለች፤ ብትሞት ግን ብዙ ፍሬ ታፈራለች። ዮሃንሰ 12፡24
ከመስቀል ውረድ የሚለውን ሰምተን በታዘዘን መጠን ስጋችን ሞቶ ለብዙዎች በረከት ለመሆን ያለንን እድል እና ክብር እናባክነዋለን፡፡
የሚያልፉትም ራሳቸውን እየነቀነቁ ይሰድቡት ነበርና። ዋ፥ ቤተ መቅደስን የምታፈርስ በሦስት ቀንም የምትሠራ፥ ከመስቀል ወርደህ ራስህን አድን አሉ። ማርቆስ 15፡29-30
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #የመንፈስፍሬ #ፍቅር #ሰላም #ስጋ #ምኞት #ማሰብ #ህይወት #ሞት #ደስታ #ዘር #ባህሪ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #የእግዚአብሄርህይወት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #በጎነት #የዋሃት #ራስንመግዛት #ትግስት #ትህትና

Thursday, March 29, 2018

ስልጣን ወይስ ባህሪ?

እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው በመልኩና በአምሳሉ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው በባህሪው እንዲኖር ነው፡፡ እግዚአብሄር የፈጠረው ሰው የእግዚአብሄር ባህሪዎች ሁሉ ነበሩት፡፡
እግዚአብሄር የፈጠረው እግዚአብሄር አታድርግ የተባለውን ያንኑ ነገር በማድረጉ የተነሳ ከእግዚአብሄር ክብር ወደቀ፡፡ ሰው እግዚአብሄርን ከመታዘዘ ይልቅ ተጨማሪ ሃይል ሲፈልግ የእግዚአብሄርን ባህሪ አጣው፡፡ ሰው በእግዚአብሄር ላይ በማመፁ እነዚያን የእግዚአብሄር ባህሪያት እንዲሁም የፈለገውን ሃይል አጣው፡፡ ሰው እንደ እግዚአብሄር ለመሆን ባለው ጥማት የእግዚአብሄርን ባህሪ አጣው፡፡  
ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ። ዘፍጥረት 3፡5
አሁንም የሰው ስጋዊ ባህሪ መልካሙን የእግዚአብሄርን ባህሪ አይፈልግም፡፡ የሰው ስጋዊ ባህሪ የሚፈልገው ሃይልን ነው፡፡ የሰው ስጋዊ ባህሪ የሚፈልገው ጊዜን መቆጣጠር እንጂ ትእግስትን አይደለም፡፡ የሰው ስጋዊ ባህሪ የሚፈልገው ሰውን መቆጣጠር እንጂ ለሌላው መገዛትን አይደለም፡፡ የሰው ስጋዊ ባህሪ የሚፈልገው ሁኔታን መቆጣጠር እንጂ ራስን መስጠት አይደለም፡፡
የሰው ስጋዊ ባህሪ የሚፈልገው ሃይሉን በትክክል የሚያስተዳድርበትን የእግዚአብሄርን ባህሪ ሳይሆን ሃይሉን ብቻ ነው፡፡ የሰው ስጋዊ ባህሪ ለሃይል ይጓጓል፡፡ የሰው ስጋዊ ባህሪ አንደኛ መሆንን እንጂ ማገልገልን አይፈልግም፡፡ የሰው ስጋዊ ባህሪ መጠቀምን እንጂ መጥቀምን አያስበውም፡፡ ስጋ ለሃይል እንጂ ለባህሪ ግድ የለውም፡፡
የዘብዴዎስ ልጆች ያዕቆብና ዮሐንስም ወደ እርሱ ቀርበው፦ መምህር ሆይ፥ የምንለምንህን ሁሉ እንድታደርግልን እንወዳለን አሉት። እርሱም፦ ምን ላደርግላችሁ ትወዳላችሁ? አላቸው። እነርሱም፦ በክብርህ ጊዜ አንዳችን በቀኝ አንዳችንም በግራህ መቀመጥን ስጠን አሉት። ማርቆስ 10፡35-37
ስጋ በነገሮች መያዝ አይፈልግም፡፡ ስጋ መታገስ አይፈልግም፡፣ስጋ መጠበቅ አይፈልግም፡፡ ስጋ ሌላወን መውደድ አይፈልም፡፡ ስጋ ሌላውን መሸከም አይፈልግም፡፡ ስጋ የሚፈልገው ሌላውን ሁሉ መለወጥን እንጂ መታገስን አይደለም፡፡ ስጋ የሚፈልገው ሌላውን መተው እንጂ መውደድ አይደለም፡፡
ስጋ መናገርን እንጂ መስማትን አይፈልግም፡፡ ስጋ በንግግር ሁሉንም መቆጣጠርን እንጂ መስማትን አይፈልግም፡፡  
ሁላችን በብዙ ነገር እንሰናከላለንና፤ በቃል የማይሰናከል ማንም ቢኖር እርሱ ሥጋውን ሁሉ ደግሞ ሊገታ የሚችል ፍጹም ሰው ነው። ያዕቆብ 3፡2
ስጋ የሚፈልገው ነገሮችን መቆጣጠር እንጂ ራሱን መስጠት አይደለም፡፡ ስጋ የሚፈልገው ሌላውን ሰው እንደርሱ ማድረግን እንጂ ሌላውን ሰው መምሰልን አይደለም፡፡ ስጋ ሌላውን ሁሉ ዝቅ አድርጎ መግዛት እንጂ ማንሳት ማስታጠቅ መልቀቅ አይፈልግም፡፡
ነፍሱን የሚያገኝ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም ስለ እኔ የሚያጠፋ ያገኛታል። ማቴዎስ 10፡39
ስጋ ተጨማሪ ሃይልን እንጂ የባህሪ ለውጥን አይፈልግም፡፡ ስጋ ተጨማሪ ስልጣንን እንጂ መገዛትን አይፈልግም፡፡
በእናንተ ዘንድ ጦርና ጠብ ከወዴት ይመጣሉ? በብልቶቻችሁ ውስጥ ከሚዋጉ ከእነዚህ ከምቾቶቻችሁ አይደሉምን? ትመኛላችሁ ለእናንተም አይሆንም፤ ትገድላላችሁ በብርቱም ትፈልጋላችሁ፥ ልታገኙም አትችሉም፤ ትጣላላችሁ ትዋጉማላችሁ ነገር ግን አትለምኑምና ለእናንተ አይሆንም፤ ትለምናላችሁ፥ በምቾቶቻችሁም ትከፍሉ ዘንድ በክፉ ትለምናላችሁና አትቀበሉም። ያዕቆብ 4፡1-3
ስለዚህ ነው ሃዋሪያው ጳውሎስ ሥጋዬን እየጎሰምሁ አስገዛዋለሁ የሚለው፡፡
ነገር ግን ለሌሎች ከሰበክሁ በኋላ ራሴ የተጣልሁ እንዳልሆን ሥጋዬን እየጎሰምሁ አስገዛዋለሁ። 1ኛ ቆሮንቶስ 9፡27
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #የመንፈስፍሬ #ፍቅር #ሰላም #ስጋ #ምኞት #ማሰብ #ህይወት #ሞት #ደስታ #ዘር #ባህሪ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #የእግዚአብሄርህይወት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #በጎነት #የዋሃት #ራስንመግዛት #ትግስት #ትህትና

አስተዳዳሪው ከሚተዳደረው ይበልጣል

እግዚአብሄር ባለጠጋ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን ለመባረክ ይፈልጋል፡፡
እግዚአብሄር ሰውን በሚባርከው በረከት ሰው ተጠቃሚ እንዲሆን እግዚአብሄር ይፈልጋል፡፡  ሰውን የሚባርከው በረከት እንዲባክን እግዚአብሄር አይፈልግም፡፡ ሰው የእግዚአብሄርን በረከት በትክክል እንዲያስተዳድረው እግዚአብሄር ይፈልጋል፡፡
ሰው የተሰጠውን በረከት በትክክል ካላስተዳደረ ያባክነዋል፡፡ ሰው የተሰጠውን በረከት የሚይዝበት ትክክለኛ አያያዝ ከሌለው በረከቱ ይባክናል፡፡
እግዚአብሄር ሰውን ከመባረኩ በፊት የበረከቱን አስተዳዳሪውን ሰውን መስራቱን የሚያስቀድመው በዚህ ምክኒያት ነው፡፡ እግዚአብሄር ስለበረከቱ ሳይሆን ስለአስተዳሪው መሰራት ትልቅ ትኩረት የሚሰጠውና የሚያስቀድመው አስተዳዳሪው ሰው ከተሰራ በረከቱን በትክክል ማስተዳደር እንደሚችል እግዚአብሄር ስለሚያውቅ ነው፡፡ አስተዳደሪው በሚገባ ከተሰራ በረከቱን ለታሰበው አላማ ሊያውለው ይችላል፡፡
ስለዚህ ነው ሰውን ከመባረኩ በፊት እግዚአብሄር የሰውን ታማኝነት የሚመዝነው፡፡ አስተዳደሪው ታማኝ ከሆነ በረከቱ ለታለመለት አላማ ይውላል፡፡ አስተዳደሪው ታማኝ እስካልሆነ ደርስ ግን ሰው ምንም ቢባረክ በሚያፈስ እቃ ውስጥ እንደተቀመጠ ፈሳሽ በረከቱ ይባክናል፡፡
የታመነ ሰው እጅግ ይባረካል፤ ባለጠጋ ለመሆን የሚቸኵል ግን ሳይቀጣ አይቀርም። ምሳሌ 28፡20
አስተዳዳሪው ሳይሰራ በፊት የተገኘ በረከት ግን ከእግዚአብሄርም ሊሆን አይችልም እንዲሁም ደግሞ ንፁህ ሊሆን አይችልም፡፡ አስተዳዳሪው ቀስ በቀስ ሳይሰራ በፊት የተገኘ በረከት መሰረት እንደሌለው ቤት ነው፡፡ አስተዳደሪው ሰው በባህሪ ሳይሰራ አስቀድሞ የተገኘ ርስት ፍፃሜው ለመልካም አይሆንም፡፡
በመጀመሪያ ፈጥኖ የተከማቸ ርስት ፍጻሜው አይባረክም። ምሳሌ 20፡21
ስለዚህ ነው ሰው ሃብቱን በትክክል ከማስተዳደሩ በፊት በባህሪ ማደግና ሃብቱን ለማስተዳደር የሚያስችለውን ብስለት ማግኘት እንዳለበት መፅሃፍ ቅዱስ የሚያስተምረው፡፡
ነገር ግን እላለሁ፥ ወራሹ ሕፃን ሆኖ ባለበት ዘመን ሁሉ፥ ምንም የሁሉ ጌታ ቢሆን ከቶ ከባሪያ አይለይም፥ ነገር ግን አባቱ እስከ ቀጠረለት ቀን ድረስ ከጠባቂዎችና ከመጋቢዎች በታች ነው። ገላትያ 4፡1-2
ርስትን ለመቀበል ሰከንድ አይፈጅም፡፡ ነገር ግን ርስትን በትክክል ለማስተዳደር የሚያበቃ ብስለትን ለማግኘት ዘመናት ይጠይቃል፡፡ 
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ኢየሱስ #ጌታ #ባህሪ #ፍቅር #ልብ #አስተዳደሪ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ወንጌል #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ

ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ 1ኛ ጢሞቴዎስ 1፡15
የሰው መንገድ በምርጫ የተሞላ ነው፡፡ ዛሬ የምንኖረው ኑሮ ትላንት የመረጥነውን ምርጫ ውጤት ነው፡፡ ወደፊት የምንኖረው ኑሮ ዛሬ የመረጥነውን ምርጫ ውጤትን ነው፡፡
ሰው በህይወቱ ዘመን ሁሉ በምድር ላይ ብዙ ምርጫ መምረጥ ቢጠበቅበትም እንደዚህ ያለ የወደፊት ህይወቱን ሁሉ የሚወስን ምርጫ ግን የለም፡፡
አንዳንድ ምርጫ በገንዘባችን ላይ ተፅእኖ ሊኖረው ይችላል፡፡ ሌላው ምርጫ በዝናችን ላይ ታላቅ ተፅእኖ ያሳድራል፡፡ ሌላው ደግሞ በጥበባችን ላይ አዎንታዊ ወይም አሉታዊን ተጽፅእኖን ያመጣል፡፡ ሌላውም በሃይላችን ላይ ተፅእኖ በማሳደር በምድር ላይ ሃያል እንድንሆን ወይም እንዳንሆን ያደርገናል፡፡ እነዚህ ሁሉ ምርጫዎች ተፅእኖ የሚያደርጉት የምድር ህይወታችንን ብቻ ነው፡፡
ነገር ግን በምድርም ከምድር ህይወት በስቲያም ህይወታችን ላይ ተፅእኖ የሚያሳድር ወሳኝ ምርጫ አለ፡፡ ሰው በምድር ላይ ሲኖር በሌላ ምርጫዎች እንኳን ቢሳሳት በዚህ ምርጫ ግን መሳሳት የለበትም፡፡ ሰው በምድር ላይ ሲኖር በሌላ ምርጫዎች የሚሳተው መሳሳት በዚህ መርጫ እንደሚሳሳተው መሳሳት አይከፋም፡፡ ሰው በሌላ ምርጫ ቢሳሳት ውጤቱ የምድር እጦት ብቻ ነው፡፡ ሰው በምድር ምርጫዎች ቢሳሳት የምርጫው ውጤት በምድር ላይ ብቻ ነው የሚቀረው፡፡
ሰው ግን በዚህ መርጫ ቢሳሳት ውጤቱ የምድርን ቢያጠቃልልም የምርጫው ውጤት በምድር ላይ ብቻ አያበቃም፡፡ ሰው በዚህ ምርጫ ቢሳሳት ውጤቱ በምድርና ከምድር ህይወት በኋላም ይቀጥላል፡፡ ሰው በዚህ መርጫ ቢሳሳት ውጤቱ የማይቀለበስ የዘላለም ነው፡፡ ሰው በዚህ መርጫ ቢሳት ውጤቱ ለዘላለም ከእግዚአብሄር መለያየትን ያመጣል፡፡
ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ 1 ጢሞቴዎስ 115
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ወንጌል #ስብከት #ቃል #የታመነ #የምድርጨው #የአለምብርሃን #ኢየሱስ #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

Wednesday, March 28, 2018

የጐመን ወጥ በፍቅር

የጐመን ወጥ በፍቅር መብላት የሰባ ፍሪዳን ጥል ባለበት ዘንድ ከመብላት ይሻላል። ምሳሌ 1517
ሰው የተፈጠረው ለእግዚአብሄር ክብር ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው ለሰላም ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው ለፍቅር ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው በሰላም እብሮ እንዲኖር ነው፡፡ ስው የተፈጠረው በፍቅር ተጋግዞ እንዶኖር ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው በሰላም ተረዳደቶ እንዶኖር ነው፡፡
ሰው ለጥል አልተፈጠረምን፡፡ ሰው ለረብሻ አልተፈጠረም፡፡ ሰው ለመነካከስ አልተፈጠረም፡፡
ስለዚህ ነው ሰው ሁሌ ሰላምን ከረብሻ የሚመርጠው፡፡ ስለዚህ ነው ሰው ሁሌ ፍቅርን ከጥላቻ የሚመርጠው፡፡ ስለዚህ ነው ሰው ሁሌ
ፍቅር የሌለው ሰው ሃብት ቢኖረው ምንም አይጠቅመውም፡፡ ሰላም የሌለው ሰው ሃያል ቢሆን ምንም አይጠቅመውም፡፡ እረፍት የሌለው ሰው ጥበብ ቢኖረው ምንም አይጠቅመውም፡፡
ስለዚህ ነው ሰው ከረብሻ ከሃብታምነት ይልቅ ሰላምን የሚመርጠው፡፡ ስለዚህ ነው ሰው ውዝግብ ዝና ይልቅ እረፍትን የሚመርጠው፡፡ ስለዚህ ነው ሰው ከእረፍት የለሽ ጥበብ ይልቅ እርካታን የሚመርጠው፡፡
የእግዚአብሄር በረከት ባለጠጋ ታደርጋለች ሃዘንም ከእርስዋ ጋር አይጨምርም፡፡
የእግዚአብሔር በረከት ባለጠጋ ታደርጋለች፥ ኀዘንንም ከእርስዋ ጋር አይጨምርም። ምሳሌ 10፡22
እግዚአብሔርን ከመፍራት ጋር ያለ ጥቂት ነገር ሁከት ካለበት ከብዙ መዝገብ ይሻላል። የጐመን ወጥ በፍቅር መብላት የሰባ ፍሪዳን ጥል ባለበት ዘንድ ከመብላት ይሻላል። ምሳሌ 15፡16-17
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ብልፅግና #የብልፅግናወንጌል #ፍቅር #ጥል #በረከት #ጎመን #ፍሪዳ #ሰላም #መሰረታዊፍላጎት #ሁሉየእናንተነውና #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #የተትረፈረፈህይወት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መርካት #ደስታ #እረፍት

ትዕግሥተኛ ሰው ከኃያል ሰው ይሻላል

ትዕግሥተኛ ሰው ከኃያል ሰው ይሻላል፥ በመንፈሱም ላይ የሚገዛ ከተማ ከሚወስድ ይበልጣል። ምሳሌ 16፡32
በምድር ላይ ሃያል የሆኑ ግን ለምድር በረከት ያልሆኑ በጣም ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ በምድር ላይ ባለጠጋ የሆኑ ነገር ግን ለምድር ስጋት የሆኑ በጣም ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ በምድር ላይ ጥበበኛ የሆኑ ነገር ግን የምድር አደጋ የሆኑ በጣም ብዙ ሰዎች ይገኛሉ፡፡
ሰው ሃይሉን ለክፋትም ይሁን ለበጎነት ሊጠቀምበት ይችላል፡፡ ሃይላችንን ለምን እንደምንጠቀምበት እስካልታወቀ ድረስ ሃይል አለን ማለት ምንም ማለት አይደለም፡፡ ስለዚህ ሃይል በማን እጅ እንዳለ ካልታወቀ ምንም ማለት አይደለም፡፡ ሃይልን ብቻ አይተህ ከተመኘኸው ሃይል ያለውን የጥፋት አቅም አልተረዳህም ማለት ነው፡፡
ሰው ባለጠጋ ነው ማለት ባለግነቱን ለክፋት እንደማይጠቀምበት ካልተረጋገጠ በስተቀር ባለጠግነቱን ብቻ የሚመኙት ነገር አይደለም፡፡ ሰው ባለጠግነቱን ለመልካም ነገር ብቻ ሳይሆን ሰውን ለመግደል ለማጎሳቆል ለመበዝበዝ ለማስለቀስ ሊጠቀምበት ይችላል፡፡
ሰው ጥቢብ ነው ማለት ጥበቡን ለክፋት አይጠቀምበትም ማለት አይደለም፡፡ ጥበብ አደጋ ሊሆን ይችላል፡፡ ጥበብ በረከት ሊሆን ይችላል፡፡ ጥበብ እንደሚይዘው ሰው ስጋት ሊሆን ይችላል፡፡
ሃያልነት ባለጠግነትና ጥበብ ከውጭ የሚሰጡ ስጦታዎች ናቸው፡፡ ሃያልነት ባለጠግነትና ጥበብ የሚያስመኩ የእድገት መለኪያዎች አይደሉም፡፡ ሃያልነት ባለጠግነትና ጥበብ የሰውን ማደግ መለወጥና መልካምነት አያሳዩም፡፡
ለሰው ሃያልነትን የሚሰጠው እግዚአብሄር ነው፡፡ ሰውን ከባለጠግነት ጋር የሚያገናኘው የእግዚአብሄር አሰራር ነው፡፡ ለሰው የጥበብን አእምሮ የሚሰጠው እግዚአብሄር ነው፡፡ ሃያልነት ባለጠግነትና ጥበብ ሃያሉን ባለጠጋውንና ጠቢቡን የሚያስመካው ምንም ነገር የለም፡፡
በመርህ መኖር ግን የሰውን የባህሪ እድገት ይጠይቃል፡፡ ትእግስት ግን የሰውን መለወጥ ይጠይቃል፡ትእግስት ግን የተሻለ መረዳትን ይጠይቃል፡፡ ትእግስት ግን ራስን መግዛትን ይጠይቃል፡፡
ሰው ሃያልነቱ የሚለካው ራሱን ሲገዛ ብቻ ነው፡፡ ሰው ሃያልነቱ የሚለካው ማድረግ የሚፈልገውን ሲያደርግ ፣ ማድረግ የማይፈለገውን ሳያደርግ ነው፡፡ የሰው ሃያልነት የሚለካው ሰው በራሱ ላይ ሙሉ ስልጣን ሲኖረው ነው፡፡ የሰው ሃያልነቱ የሚለካው ራሱን ሲመራ ብቻ ነው፡፡  
ሰው ባለጠግነቱ የሚለካው በውስጡ ባለጠጋ ሲሆን ነው፡፡ ሰው ባለጠግነቱ የሚለካው በሰላም ፣ በደስታ ፣ በእረፍትና በእርካታ ባለጠጋ ሲሆን ነው፡፡ ሰው ባለጠግነቱ የሚለካው በነፍሱ ባለጠጋ ሲሆን ነው፡፡
ወዳጅ ሆይ፥ ነፍስህ እንደሚከናወን፥ በነገር ሁሉ እንዲከናወንልህና ጤና እንዲኖርህ እጸልያለሁ። 3ኛ ዮሐንስ 1፡2
ሰው ባለጠግነቱ የሚለካው በይቅርታና እና በምህረት ባለጠጋ ሲሆን ነው፡፡ የሰው ባለጠግነት የሚለካው ለራሱ ነገሮችን በራስ ወዳድነት በማግበስበስ ሳይሆን በመልካም ስራ ባለጠጋ ሲሆን ነው፡፡
እውነተኛውን ሕይወት ይይዙ ዘንድ፥ ለሚመጣው ዘመን ለራሳቸው መልካም መሠረት የሚሆንላቸውን መዝገብ እየሰበሰቡ፥ መልካምን እንዲያደርጉ በበጎም ሥራ ባለ ጠጎች እንዲሆኑ፥ ሊረዱና ሊያካፍሉም የተዘጋጁ እንዲሆኑ ምከራቸው። 1ኛ  ጢሞቴዎስ 6፡18-19
ሰው ጠቢብነቱ የሚታወቀው እግዚአብሄርን በመፍራት ከእግዚአብሄርና ከሰው ጋር በትግስትና በትህትና ሲኖር ነው፡፡ ሰው ጠቢብነቱ የሚታወቀው በመጀመሪያ ከፈጠረው ጋር እንዴት በትህትና እንደሚኖር ሲያውቅ ነው፡፡ ሰው ጠቢብነቱ የሚታወቀው በህይወቱ እጅግ አስፈላጊ ለሆነው ለፈጠረው ለሰራው ለእግዚአብሄር እውቅና መስጠቱ ነው፡፡ ሰው ጠቢብነቱ የሚለካው ለእግዚአብሄር የመጀመሪያውን ስፍራ ሲሰጥ ነው፡፡
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ሰነፎች ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ። ምሳሌ 1፡7
ስለዚህ ነው ትእግስተኛ ሰው ከሃያል ስው ይሻላል የሚባለው፡፡
ትዕግሥተኛ ሰው ከኃያል ሰው ይሻላል፥ በመንፈሱም ላይ የሚገዛ ከተማ ከሚወስድ ይበልጣል። ምሳሌ 1632
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ኢየሱስ #ጌታ #ባህሪ #ፍቅር #ልብ #የዋህ #ዝግተኛ #የመንፈስፍሬ #ውበት #የልብሰው #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ወንጌል #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Tuesday, March 27, 2018

የአፅናኙ መንፈስ ቅዱስ አምስት እጥፍ በረከቶች

አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ (አፅናኝ ፣ ተሟጋች ፣ የሚማልድ አማካሪ ፣ አብሮ የሚቆም ) እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል። ዮሐንስ  14:26
ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ እንደአባት ነበር፡፡ እንደአባት ይመራቸዋል ያስተምራቸዋል ይመክራቸዋል፡፡ ኢየሱስ በምድር በነበረ ጊዜ ስጋ ለብ ስለመጣ ውስን በመሆኑ ይህንን ሊያደርግ የቻለው ለደቀመዛሙርቱ ብቻ ነበር፡፡ ኢየሱስ ከምድር ላይ ሲወሰድ ደቀመዛሙርቱን አባት እንደሌላቸው ልጆች እንደማይተዋቸውና አጽናኙ መንፈስ ቅዱስ እንደሚመጣና እንደሚመራቸው ይነግራቸው ነበር፡፡ መንፈስ ቅዱስ ሲመጣ እና በአማኙ ውስጥ ሲኖር የሚያደርጋቸውን አምስት ነገሮችን እንመልከት፡፡
1.      አፅናኝ
ኢየሱስን ስንቀበል እና መንፈስ ቅዱስ በእኛ ውስጥ ሲኖር የሚያደርገው ነገር እኛን ማፅናናተ ነው፡፡ ማፅናናተ ማለት ደግሞ ህይወታቸንነ ማመቻቸት የተመቻቸ ሁኔታን መፍጠር የሚቆረቁረንን ነገር ማወገድ እንቅፋትን ከፊታችን ማስወገድ ማጽፅናናት ደስ ማሰኘትና በደስታ እና በስኬት ጌታን እንድንከተል ማስቻል የመንፈስ ቅዱስ ስራ ነው፡፡
ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤ ዮሃንስ 14፡15-16
2.     ተሟጋች
መንፈስ ቅዱስ ጠበቃችን ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ በእኛ ወገን ሆኖ ነገሮችን እና ሁኔታዎችን እንዴት እንደምናልፍ ይቆምልናል፡፡ እኛ መናገር ባልቻልን ጊዜ መንፈስ ቅዱስ አፋችንን ተጠቀሞ ይናገርልናል፡፡ በህይወት ሁኔተ ውስጥጭ በተግዳሮት ውስጥ የእኛ ወገን ሆኖ ምን ማድረግ እንዳለብን እንደጠበቃ ያማክረናል ይመራናል፡፡
አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና። ማቴዎስ 10፡19-20
3.     የሚማልድ
መንፈስ ቅዱስ ምን መፀለይ እንዳለብን በማናውቅበት ጊዜ እንኳን ያለማወቅ ድካችንን ያግዛል፡፡ ፀሎታችን ከንቱ አንዳይሆን ይረዳል፡፡ ፀሎታችን የእግዚአብሄርን ልብ ያማከለ እንዲሆን ያደርጋል፡፡ ጸሎታችን ፍሬያማ እንዲሆን ያደርጋል፡፡
እንዲሁም ደግሞ መንፈስ ድካማችንን ያግዛል፤ እንዴት እንድንጸልይ እንደሚገባን አናውቅምና፥ ነገር ግን መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት ይማልድልናል፤ ሮሜ 8፡26
4.     አማካሪ
ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረ ጊዜ ድንቅ መካር ነበር፡፡ አሁን መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ድንቅ መካር ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ የሚመክረው ምክር መሬት ጠብ የማይል ምክር ነው፡፡
እናንተስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ ይኖራል፥ ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም፤ ነገር ግን የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉ እንደሚያስተምራችሁ፥ እውነተኛም እንደ ሆነ ውሸትም እንዳልሆነ፥ እናንተንም እንዳስተማራችሁ፥ በእርሱ ኑሩ። 1ኛ ዮሃንስ 2፡27
5.     አብሮ የሚቆም
መንፈስ ቅዱስ ሁሌ አብሮን ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ የተሰጠን ለዘላለም ከእኛ ጋር አብሮ እንዲኖር ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ አልነበረም ብለምን የምናመካኝበት ጊዜ የለም፡፡ መንፈስ ቅዱስ በየጊዜው አይጎበኘንም፡፡ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ይኖራል፡፡  
ይናገርበት የነበረውንም ጥበብና መንፈስ ይቃወሙ ዘንድ አልቻሉም። ሐዋሪያት 6፡10
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #መንፈስቅዱስ #አፅናኝ #የሚማልድ #አማካሪ #ተሟጋች #ጠበቃ #እውነት #በውስጣችሁ #መንፈስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #ቅባት #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መውደድ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች

ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤ እርሱም ዓለም የማያየውና የማያውቀው ስለ ሆነ ሊቀበለው የማይቻለው የእውነት መንፈስ ነው፤ ነገር ግን ከእናንተ ዘንድ ስለሚኖር በውሥጣችሁም ስለሚሆን እናንተ ታውቃላችሁ። ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ። ዮሃንስ 14፡15-18
ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረ ጊዜ ደቀመዛሙርቱን ያስተምራቸውና ይመራቸው ነበር፡፡ ጥያቄ ሲኖርባቸው ጥያቄያውን በትክክል ይመልስላቸው ነበር፡፡ ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱን እንደአባት ወደ እውነት ሁሉ ይመራቸው ነበር፡፡
ኢየሱስ የምድር አገልግሎቱን ጨርሶ በሚወሰድበት ጊዜ ግን ደቀመዛሙርቱ የኢየሱስን የአባትነት መሪነት ያጡታል፡፡ ኢየሱስ ወደሰማይ ሲወሰድ በግል እያንዳንዳቸውን አግኝቶ ሊመክራቸ ወደ እውነት ሁሉ ሊመራቸው አይችልም ነበር፡፡ ስለዚህ ነው ኢየሱስ ከምድር ከመሄዱ በፊት አባት እንደሌላቸው ልጆች ካለ ምሪትና ካለ ማፅናናት እንደማይተዋቸው በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ተመልሶ እንደሚመጣ ለደቀመዛሙርቱ የሚነግራቸው፡፡
አሁን መንፈስ ቅዱስ በምድር ላይ አለ፡፡ አሁን መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን በሚከተሉ ሰዎች ውስጥ ያድራል፡፡ አሁን መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ያደርገው የነበረውን ማፅናትና ምሪት ሁሉ ይሰጣል፡፡
ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረ ጊዜ ሊያፅናና ፣ ሊመክር ፣ ሊያስተምርና ወደ እውነት ሁሉ ሊመራ የሚችለው ጥቂት ሰዎችን ብቻ ነበር፡፡ ኢየሱስ በምደር ሲኖር በስጋ የተወሰነ ስለነበር የምድር ህዝብን ሁሉ በግል ሊያፅናናና ሊመራ አይችልም ነበር፡፡  
አሁን መንፈስ ቅዱስ ግን በስጋ ስለማይኖርና በስጋ ስለማይወሰን ኢየሱስን የተቀበሉት ሰዎች ሁሉ ውስጥ ይኖራል፡፡ ኢየሱስን በሚከተሉት ሰዎች ሁሉ ውስጥ በመኖር ወደ እውነት ሁሉ ይመራቸዋል፡፡
እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤ እርሱም ዓለም የማያየውና የማያውቀው ስለ ሆነ ሊቀበለው የማይቻለው የእውነት መንፈስ ነው፤ ነገር ግን ከእናንተ ዘንድ ስለሚኖር በውሥጣችሁም ስለሚሆን እናንተ ታውቃላችሁ። ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ። ዮሃንስ 14፡15-18
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #መንፈስቅዱስ #አፅናኝ #እውነት #በውስጣችሁ #መንፈስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #ቅባት #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መውደድ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ