Popular Posts

Saturday, January 6, 2018

ለፍጻሜሽም ተስፋ አለ፥ ይላል እግዚአብሔር

ለፍጻሜሽም ተስፋ አለ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ ልጆችሽም ወደ ዳርቻቸው ይመለሳሉ። ኤርምያስ 3117
ሰው ለእግዚአብሄር ክብር ታስቦና ታቅዶ በእግዚአብሄር መልክና አምሳል ተፈጥሮአል፡፡
እግዚአብሔርም አለ፦ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ። እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ እንዲህም አላቸው፦ ብዙ፥ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት፥ ግዙአትም፤ የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ግዙአቸው። ዘፍጥረት 1፡26፣28
ሰው ከመፈጠሩ በፊት ለምን እንደሚፈጠር እግዚአብሄር ጠንቅቆ ያውቅ ነበር፡፡ ሰው ድንገት አልተፈጠረም፡፡ ወይም ሰው አላማ የተፈለገለት ከተፈጠረ በኋላ አይደለም ፡፡ ሰው ከመፈጠሩ በፊት የተፈጠረለት በቂ አላማ ነበረው፡፡ ሰው የመፈጠሩ ምክኒያት ያንን የተፈጠረለትን አላማ እንዲፈፅም ነው፡፡
እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን። ኤፌሶን 2፡10
ስለዚህ ሰው ወደ ምድር የመጣው የሚደርስበት ቦታ እና ግቡ ታውቆ ነው፡፡ እግዚአብሄር የመጨረሻውን ከመጀመሪያ ያያል፡፡
በመጀመሪያ መጨረሻውን፥ ከጥንትም ያልተደረገውን እነግራለሁ፤ ምክሬ ትጸናለች ፈቃዴንም ሁሉ እፈጽማለሁ እላለሁ። ኢሳያስ 46፡10
ድንገት ወደምድር የመጣ አንድም ሰው የለም፡፡ በምድር ላይ የምናየው ማንኛውም ሰው ይረዳውም አይረዳውም ወይም ይከተለውም አይከተለውም የእግዚአብሄርን የተለየ አላማ ለማስፈፀም ተወልዶዋል፡፡
እግዚአብሄር የህይወት ፍፃሜያችንን የሚሰራው በየጊዜው የፀሎት ርእሳችንን እየሰበሰበና እያሰበበት አይደለም፡፡ እኛ ወደምድር ከመምጣታችን በፊት ወደምድር የመጣንለት እኛ ብቻ የምንፈፅመው ልዩ አላማ አለ፡፡ ወደ ምድር የመምጣታችን ምልክቱ በስማችን የተዘጋጀ የህይወት አላማ መኖሩ ነው፡፡
 እኔ ለእውነት ልመሰክር ስለዚህ ተወልጃለሁ ስለዚህም ወደ ዓለም መጥቻለሁ፤ ዮሐንስ 18፡37
ተስፋ ያለን የፍፃሜ ሰዎች ነን፡፡
ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። ኤርሚያስ 29፡11
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ራእይ #እይታ #አላማ #ተስፋ #ፍፃሜ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ተሰፋ #ፍፃሜ #የእግዚአብሄርሃሳብ #የእግዚአብሄርእቅድ #የእግዚአብሄርፈቃድ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment