Popular Posts

Friday, January 12, 2018

በነገር ሁሉ እንዲከናወንልህ - ከውስጥ ወደ ውጭ የሆነ ክንውን

ወዳጅ ሆይ፥ ነፍስህ እንደሚከናወን፥ በነገር ሁሉ እንዲከናወንልህና ጤና እንዲኖርህ እጸልያለሁ። 3 ዮሐንስ 1፡2
እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው በለመልኩና በአምሳሉ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው በክብሩ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው ለክንውን ነው፡፡ እግዚአብሄር ለውድቀት የፈጠረው ሰው አልነበረም፡፡
ሰው በሃጢያት ምክንያት ክንውንን ከህይወቱ አጣው፡፡
ኢየሱስ ወደምድር የመጣው የሃጢያታችንን እዳ ሁሉ ለመክፈልና የእግዚአብሄር ልጅነትን ክንውን በህይወታችን ሊመልስ ነው፡፡
እውነተኛ ክንውን ደግሞ የሚጀምረው ከውስጥ ነው፡፡ ሰው ሲከናወንለት መጀመሪያ በነፍሲ ይከናወንለታል፡፡ በውጭው የሚከናወንለት ሰው ተከናወነለት አይባል፡፡ ነፍሱ ያልተከናወነችና በነፍሱ የተቀብዘበዘ ክንውኑ የውሸት ክንውን ነው፡፡ እግዚአብሄር ውጫችን እንዲከናወን የሚፈልገው የውጭውን ክንውን የሚሸከመው ውስጣችን በተከናወነ መጠን ነው፡፡ የውጭውን ክንውን የሚያስተዳደረው የውስጣችን ባህሪያን በተሰራና ባደገ መጠን ውጫችን እንዲከናወን እግዚአብሄር ይፈልጋል፡፡  
ታላቁና ክንውን የነፍስ ክንውን ነው፡፡ ታላቁ ክንውን የነፍስ ነፃ መውጣት ነው፡፡ ትልቁ ክንውን የነፍስ ከጥላቻ ከመራርነት ከመቅበዝበዝ ነፃ መውጣት ነው፡፡
የነፍስ ክንውን መገለጫዎች
ፍቅር
በፍቅር የሚመላለስ ሰው እውነተኛ የተከናወነለት ሰው ነው፡፡ በጥላቻ የሚኖር ሰው በእስራት ይኖራል፡፡ በጥላቻ የሚኖር ሰው በጨለማ ይኖራል፡፡ በጥላቻ የሚኖር ሰው በስቃይና በጉስቁልና ይኖታል፡፡  
እኛም እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር አውቀናል አምነንማል። እግዚአብሔር ፍቅር ነው፥ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል። 1ኛ ዮሐንስ 4፡16
ሰላም
ሰው ሰላም ካለው ሃብታም ነው፡፡ ሰላም የሌላው ሰው ምንም ቢኖረው ጎስቋላ ነው፡፡ ሰው ሰላም ከሌለው ደካማ ነው አቅምም የለውም፡፡
በአንድ አካልም የተጠራችሁለት ደግሞ የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይግዛ፤ የምታመሰግኑም ሁኑ። ቆላስይስ 3፡15
እርካታ
ሰው ባለው ነገር ካልረካ በጉድለት ይኖራል፡፡ ሰው ባለው ነገርና በደረሰበት ደረጃ ራሱን ካማጠነና ከረካ በነፃነት ይኖራል፡፡
ነገር ግን በሁሉ እንደ እግዚአብሔር አገልጋዮች ራሳችንን እናማጥናለን፤ 2 ቆሮንቶስ 6፡4
ደስታ
የልብ ደስታ የሌለውና የሚያዝን ሰው ደካማ ይሆናል፡፡ የልብ ደስታ ሃይላችን ነው፡፡ ሰው በጌታ ያለው ደስታ ከምንም ሃዘን በላይ ከሆነ እንዳይጎዳ ይጠብቀዋል፡፡ ሰው በምድራዊ ማግኘትና ማጣት ደስታው ከፍና ዝቅ የማይል ሰው የተከናወነለት ሰው ነው፡፡   
ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ። ፊልጵስዩስ 4፡4
ምሪት
ምሪት ያለው ሰው የት እንዳለ ወደየት እንደሚሄድ የሚያውቅ ሰው ብርሃን አለው፡፡ ሰው ግን የሚሄድበትን ካላወቀ ሲደርስም አያውቅም፡፡ ሰው የሚሄድበትን ካላወቀ መቼ እንደሚሰናከል አያውቅም፡፡
ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ እግሩንም የሚያፈጥን ከመንገድ ይስታል። ምሳሌ 19፡2
የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ። ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤ ኤፌሶን 1፡17-19
የልብ ንፅህና
ሰው መሃሪና ይቅር ባይ ካልሆነ አልተከናወነለትም፡፡ ልቡ ንፁህ ላልሆነ ሰው እውነተኛ ክንውን የማይታሰብ ነው፡፡
ስለዚህ ርኵሰትን ሁሉ የክፋትንም ትርፍ አስወግዳችሁ፥ ነፍሳችሁን ማዳን የሚችለውን በውስጣችሁም የተተከለውን ቃል በየዋህነት ተቀበሉ። ያዕቆብ 1፡21
እምነት
ሰው እግዚአብሄርን ካመነ የተከናወነለት ሰው ነው፡፡
ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና። እብራዊያን 11፡6
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ብልፅግና #የብልፅግናወንጌል #ደስታ #እርካታ #ሰላም #ምሪት #ፍቅር #እምነት #መፀለይ #ሞገስ #በረከት #ስኬት #እረኛእግዚአብሄር #ስምረት #መሰረታዊፍላጎት #ሁሉየእናንተነውና #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #የተትረፈረፈህይወት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መርካት #ደስታ #የልብስፋት #ማስተዳደር #እረፍት

No comments:

Post a Comment