Popular Posts

Saturday, October 14, 2017

ፈትኑኝ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በዚህ ፈትኑኝ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፡፡ ሚልክያስ 3፡10
እግዚአብሄር እውነተኛ አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሄር መልኩ አንድና አንድ ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄር አይለወጥም፡፡ እግዚአብሄር አይዋሽም፡፡ እግዚአብሄር ታላቅ ነው፡፡ እግዚአብሄር የሚፈራው የለም፡፡ እግዚአብሄ ቅዱስ ነው፡ሸ እግዚአብሄ ንፁህ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሊደብቀው የሚፈልገው ነገር የለም፡፡ እግዚአብሄር አውነትን ይናገራል፡፡
የእግዚአብሄ ቃል እውነት ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል የተፈተነ ነው፡፡ የእግዚአብሄ ቃል ተፈትኖ ያለፈ አስተማማኝ ማነም ሰው ሊደገፍበት የሚችል ነው፡፡  
በምድር ላይ እንደ ተፈተነ ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ ብር የእግዚአብሔር ቃላት የነጹ ቃላት ናቸው። መዝሙር 12፡6
ስለዚህ ነው እግዚአብሄር ፈትኑኝ የሚለው፡፡ ስለዚህ ነው እግዚአብሄር ያልፈፀምኩት ቃል የት አለ? ኑና እንዋቀስ የሚለው፡፡ እግዚአብሄ ቃሉን ሁልጊዜ ስለሚጠብቅ ከማንም ጋር ለመዋቀስ አይፈራም፡፡ እግዚአብሄር ቃሉን ሙሉ ለሙሉ ስለሚጠብቅ ኑና እንዋቀስ ይላል፡፡ እግዚአብሄር የማንም ባለእዳ አይደለም፡፡
ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር፤ ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች፤ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች። ኢሳያስ 1፡18
እግዚአብሄር መጠየቅን አይፈራም፡፡ እግዚአብሄር በቃሉ መፈተንን ይወደዋል፡፡ እግዚአብሄር እውነተኛ ስለሆነ ሁልጊዜ በቃሉ እንድንፈትነው ይጋብዘናል፡፡
በዚህ ፈትኑኝ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፡፡ ሚልክያስ 3፡10
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#እምነት #ማየት #አለማየት #ቃል #የእምነትተጋድሎ #የእግዚአብሄርቃል #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment