Popular Posts

Friday, October 27, 2017

በፍቅሬ ኑሩ

አብ እንደ ወደደኝ እኔ ደግሞ ወደድኋችሁ፤ በፍቅሬ ኑሩ። እኔ የአባቴን ትእዛዝ እንደ ጠበቅሁ በፍቅሩም እንደምኖር፥ ትእዛዜን ብትጠብቁ በፍቅሬ ትኖራላችሁ። ዮሐንስ 15:9-10
ኢየሱስ እንዲህ እያለ ነው፡፡ በፍቅሬ ብሉ ፣ በፍቅሬ ጠጡ ፣ በፍቅሬ ግቡ ፣ በፍቅሬ ውጡ ፣ በፍቅሬ ጠንክሩ ፣ በፍቅሬ ተከናወኑ ፣ በፍቅሬ ጥግቡ ፣ በፍቅሬ በርቱ ፣  በፍቅሬ ተደገፉ ፣ በፍቅሬ ተማመኑ ፣ በፍቅሬ ተስፋ አድርጉ ፣ በፍቅሬ እረፉ ፣ በፍቅሬ ስሩ . . .
ሰው ለመኖር መኖሪያ ያስፈልገዋል፡፡ ሰው መኖሪያ ከሌለው መኖር አይችልም፡፡ ሰው ለመኖር ህይወት የሚጠይቃቸውን ሁኔታዎችን ተቋቁሞ ማለፍ አለበት፡፡ ሰው በምድር ላይ ለመኖር አቅራቦት ያስፈልገዋል፡፡ ሰው ለመኖር ሃይል ያስፈልገዋል፡፡ ሰው ለመኖር ጥንካሬ ያስፈልገዋል፡፡ ሰው ለመኖር ምሪት ያስፈልገዋል፡፡ ሰው ለመኖር ፍቅር ያስገፈልገዋል፡፡
አብ ኢየሱስን ይወደዋል፡፡ ኢየሱስ በምድር ላይ የኖረው በአብ ፍቅር ነው፡፡ ኢየሱስ በምድር ላይ የተከናወነው በአብ ፍቅር ነው፡፡ ኢየሱስ በምድር ላይ የወጣውና የገባው አላማውንም የፈፀመው በአብ ፍቅር ነው፡፡ ኢየሱስ በምድር ላይ የረካው በአብ ፍቅር ነው፡፡ ኢየሱስ በምድር ላይ መከራን የተጋፈጠው በአብ ፍቅር ነው፡፡
ኢየሱስ እኔን ምሰሉ እያለን ነው፡፡ እኔ በአብ ፍቅር እንደኖርኩና እንዳሸነፍኩ እናንተም በእኔ ፍቅር ኑሩ ውጡ ግቡ አሸንፉ እያለን ነው፡፡
ለመኖር ለመውጣት ለመግባት የህይወት አላማን ለማሳካት እግዚአብሄር ፍቅር መሆኑን ከማወቅ በላይ የሆነ እውቀት የለም፡፡ ማስተዋሉ የማይመረመር እግዚአብሄር ፍቅር ነው፡፡ ሁሉን ቻይ የሆነው እግዚአብሄር ይወደናል፡፡ የዘላለም አምላክ አቅራቢያችን ነው፡፡
በእግዚአብሄር ፍቅር መኖር ካልቻልን በምንም ነገር መኖር አንችልም፡፡ በእግዚአብሄር ፍቅር ከኖርን ደግሞ የማናደርገው ነገር አይኖርም፡፡ በእግዚአብሄር ፍቅር ከኖርን የማንደርስበት ከፍታ የለም፡፡ በእግዚአብሄር ፍቅር ከኖርን የማናገኘው መልካም ነገር የለም፡፡ በእግዚአብሄር ፍቅር ከኖርን የማንሆነው ነገር የለም፡፡
አብ እንደ ወደደኝ እኔ ደግሞ ወደድኋችሁ፤ በፍቅሬ ኑሩ። ዮሐንስ 15:9
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ፍቅር #መውደድ #ኑሩ #ህይወት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #ቸርነት #ትግስት #ፍርሃት #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #መውደድ #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment