Popular Posts

Friday, September 29, 2017

እንደ እርሱ ያለ ረዳት

አዳምም ለእንስሳት ሁሉ፥ ለሰማይ ወፎችም ሁሉ፥ ለምድር አራዊትም ሁሉ ስም አወጣላቸው፤ ነገር ግን ለአዳም እንደ እርሱ ያለ ረዳት አልተገኘለትም ነበር። ዘፍጥረት 2፡20
እግዚአብሄር ሰውን ከፈጠረ በኋላ ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም በማለት የሚመቸውን ረዳት እንፍጠርለት ሲል እንመለከታለን፡፡ ከዚያም እግዚአብሄር የምድርን እንስሳትን ሁሉ በምን ስም እንደሚጠራቸው ያይ ዘንድ በፊቱ አሳለፈለት፡፡ ሰው ግን ለሁሉም ስም ካወጣ በኋላ ብቸኛ ነበር፡፡ ለሰው ግን እርሱንም የሚመስል እንደ እርሱ የሚያስብ እንደ እርሱ የሚናገር እንደ እርሱ የሚሰው አልተገኘለትም ነበር፡፡ ለአዳም እንደ እርሱ ያለ ረዳት አልተገኘለትም ነበር፡
በተመሳሳይ መልኩ እግዚአብሄር ሁሉንም ነገር ከፈጠረ በኋላ እንደእርሱ ያለ ረዳት አልተገኘለትም ነበር፡፡ እግዚአብሄር ሁሉን ከፈጠረ በኋላ ወንድና ሴት ልጆች የቤተሰቡ አባል አልነበሩም ነበር፡፡ ስለዚህ ነው እግዚአብሄር ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር ብሎ የተናገረው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው እርሱን የሚመስል ፣ ከእርሱ ጋር የሚግባባ ፣ እንደ እርሱ የሚሰማው ፣ እንደ እርሱ የሚያስብ እንደ እርሱ ያለ ወዳጅ ፈልጎ ነው ፡፡
እግዚአብሄር ሰውን ሳይሰስት በመልኩና በአምሳሉ የፈጠረው እርሱን የሚረዳው እንደ እርሱ ያለ ረዳት ፈልጎ ነው፡፡
እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው። ዘፍጥረት 1፡27
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #በክርስቶስ #መንፈስ #ነፍስ  #መልክ #አምሳል #የእግዚአብሄርልጅ #ወዳጅ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ማየት #የእግዚአብሄርመንግስት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አዲስፍጥረት #ክርስቶስ #የእግዚአብሄርቤተሰብ #ማእረግ #ስልጣን #ዳግመኛመወለድ

No comments:

Post a Comment