Popular Posts

Friday, September 22, 2017

የእውቀት ማጣት አደጋ

ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ ምሳሌ 192
ኢየሱስ በመስቀል ላይ የከፈለልንን የሃጢያት ዋጋ ለእኔ ነው ብለን ስንቀበል እግዚአብሄር ይቀበለናል፡፡ እግዚአብሄር ያዘጋጀውን የመዳኛ መንገድ የመስቀል ስራ ስንቀበል ዳግመኛ እንወለዳለን፡፡ ሰው ከእናትና አባቱ በስጋ ሲወለድ ወደዚህ ምድር ይገባል፡፡ ሰው ደግሞ የእግዚአብሄርን ቃል ሰምቶ ሲቀበል ዳግመኛ ይወለዳል፡፡
ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም። ዮሃንስ 1፡12-13
በክርስቶስ የሆነ ሰው አዲስ ፍጥረት ነው፡፡ ሰው ዳግመኛ ሲወለድ መንፈሱ አዲስ ነው፡፡
ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል። 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡17
ሰው አዲስ ፍጥረት ቢሆንም በነፍሱ ውስጥ ለዘመናት የተቀመጠ አለማዊ እውቀት ብንን ብሎ አይጠፋም፡፡ ዳግመኛ የተወለደው ሰው አሮጌውን የአለም እውቀት በአዲሱ የእግዚአብሄር ቃል እውቀት መተካት ይገባዋል፡፡ ዳግም የተወለደው ሰው ነፍስ አለማዊ እውቀት በቃሉ እውቀት ካልተተካ ሰው ዳግመኛ ተወልዶ እንደ አለማዊ ሰው በሃጢያት እና በሽንፈት ሊኖር ይችላል፡፡ ነፍስ ካለቃሉ እውቀት ከሆነች በምታውቀው በአለማዊ አሰራር እውቀት ብቻ ስለምትኖር መለወጥ ያቅታታል፡፡ ነፍስ በእግዚአብሔር ቃል እውቀት ከአለማዊ እውቀት መዳን አለባት፡፡
ስለዚህ ርኵሰትን ሁሉ የክፋትንም ትርፍ አስወግዳችሁ፥ ነፍሳችሁን ማዳን የሚችለውን በውስጣችሁም የተተከለውን ቃል በየዋህነት ተቀበሉ። ያዕቆብ 1፡21
ነፍስ የእግዚአብሄር ቃል እውቀት ከሌላት ለእግዚአብሄር መኖር ያቅታታል፡፡ የእግዚአብሄር መንግስት አሰራርና የአለም አሰራር እጅግ ስለሚለያይ ነፍስ የእግዚአብሄር ቃል እውቀት ከሌላት በምድር ላይ የተጠራችበትን አላማ መፈፀም ያቅታታል፡፡  
ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ ምሳሌ 19፡2
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እውቀት #ጥበብ #ነፍስ #መዳን #ኢየሱስ #ጌታ #እግዚአብሔር #እውቀት #መልካም #መታዘዝ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #አእምሮ #ሰላም #ማስተዋል #ልጅ

No comments:

Post a Comment