Popular Posts

Wednesday, September 20, 2017

ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም

ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም
ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ ምሳሌ 19፡2
ኢየሱስ በመስቀል ላይ የሰራልንን የደህነት ስራ በማመን ኢየሱስን ከተቀበልን በኋላ በክርስቶስ እንዴት እንደምንኖር ማወቅ ወሳኝ እርምጃ ነው፡፡ ሰው በቃሉ እውቀት ነፍሱን ካላደሰ ጌታን ተቀብሎ እንዳልተቀበለ ሰው በአሮጌ ማንነቱ ሊኖር ይችላል፡፡
ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥ በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፥ ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ። ኤፌሶን 4፡22-24
ሰው በሃጢያት ምክኒያት አስተሳሰቡ ተበላሽቶዋል፡፡ ሰው ኢየሱስን ተቀብሎ በእግዚአብሄር ቃል እውቀት ነፍሱን ካላዳናት በስተቀር የሰይጣን እስረኛ ሆና ልትቆይ ትችላለች፡፡ ሰው ኢየሱስን ተቀብሎ በእግዚአብሄር ቃል እውቀት ካልታጠቀ የእግዚአብሄርን አላማ በህይወቱ ሊፈፅም አይችልም፡፡ ሰው ከልጅነቱ በተለያየ መንገድ የሰማው እንደ እግዚአብሄር ቃል ያልሆነ የአለም አሰራር በነፍሱ ውስጥ አለ፡፡ ሰው ዳግመኛ ከእግዚአብሄር ቃል ተወልዶ ወደ እግዚአብሄ ምንግስት ሲገባ በእግዚአብሄር ቃል ነፍሱን ማደስ አለበት፡፡ ነፍሱን በእግዚአብሄር ቃል የሚያድስ ሰው ብቻ ነው ነፍሱን ከአለማዊ ክፉ አስተሳሰብና ከሰይጣን ጥቃት የሚያድናት፡፡
ስለዚህ ርኵሰትን ሁሉ የክፋትንም ትርፍ አስወግዳችሁ፥ ነፍሳችሁን ማዳን የሚችለውን በውስጣችሁም የተተከለውን ቃል በየዋህነት ተቀበሉ። ያዕቆብ 1፡21
ሰው በክርስቶስ ከእግዚአብሄር ጋር ታርቆ እንደባይተዋር ሊኖር ይችላል፡፡ ሰው የእግዚአብሄር ልጅ ሆኖ እውቀት ከሌላው በሽንፈት ሊኖር ይችላል፡፡ ሰው በክርስቶስ ወደ እግዚአብሄር መንግስት ተቀላቅሎ ሳለ የእግዚአብሄር ቃል እውቀት ከሌለው የእግዚአብሄርን አላማ በህይወቱ ሳይፈጽም እንደ ማንኛውም ተራ ሰው ኖሮ ሊያልፍ ይችላል፡፡
ሰው ግን ክቡር ሆኖ ሳለ አያውቅም፤ እንደሚጠፉ እንስሶች መሰለ። መዝሙር 49፡12
ኢየሱስን ለተቀበለ ሰው በክርስቶስ ታላቅ አርነት ተዘጋጅቶለት እያለ የቃሉ እውቀት ከሌለው በእስራት ሊኖር ይችላል፡፡ የኢየሱስን አዳኝነት መቀበል ለመዳን የመጀመሪያው ደረጃ ቢሆንም ሰው እውነትን አውቆ ካልኖረበት ነፃ መውጣት በፍፁም አይችልም፡፡
ኢየሱስም ያመኑትን አይሁድ፦ እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤ እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው። ዮሃንስ 8፡21-32
እግዚአብሄር በክርስቶስ ሁሉን ስላዘጋጀልን ከእኛ የሚጠበቀው እግዚአብሄርንና ክርስቶስን በማወቅ ፀጋና ሰላም እንዲበዛል ነው፡፡
የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ። 2ኛ ጴጥሮስ 1፡2-3
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እውቀት #ጥበብ #ነፍስ #መዳን #ኢየሱስ #ጌታ #እግዚአብሔር #ንስሃ #መልካም #መታዘዝ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #አእምሮ #ሰላም #ማስተዋል #ልጅ

No comments:

Post a Comment