Popular Posts

Monday, April 24, 2017

ማንም ያለው ነገር

እውነት እላችኋለሁ፥ ማንም ያለው ነገር እንዲደረግለት ቢያምን በልቡ ሳይጠራጠር፥ ይህን ተራራ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ቢል ይሆንለታል። ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ፥ ይሆንላችሁማል። ማርቆስ  11፡23-24
የእግዚአብሄር ልጅነት ክብር ታላቅ ክብር ነው፡፡ የእግዚአብሄር ልጅ ንግግር ታላቅ ሃይል ያለው ንግግር ነው፡፡ የእግዚአብሄር ልጅ የእምነት ቃል ሃያል ቃል ነው፡፡
ማንም ያለው ነገር እንዲደረግለት ቢያምን ይሆንለታል፡፡  
የምንለው ነገር ይሆናል፡፡ የእግዚአብሄር ልጅነታችንን ስልጣን የምንገልፀው በመናገር ነው፡፡ በንግግራችን ውስጥ ታላቅ ስልጣን  አለ፡፡
ለንግግራችን ሃይል የሚሰጠው እምነታችን ነው፡፡
በንግግር የሚገለፅ እምነት ነገሮችን ይለውጣል፡፡ አምነን የምንናገረው ነገር ይሆናል፡፡ አምነን የምናዘው ተራራ ይታዘዛል፡፡
እምነትን የሚያመጣው ደግሞ የእግዚአብሄርን ቃል መረዳታችን ነው፡፡ እምነት የሚመጣው የእግዚአብሄርን ቃል ከመስማት ነው፡፡ እምነት የእግዚአብሄርን ቃል እውነት ነው ብሎ መቀበል ነው፡፡ እምነት የሚመጣው የእግዚአብሄርን ቃል በመቀበል ነው፡፡
እምነትን የሚያጠፋውን ጥርጥርን ደግሞ መዋጋት አለብን፡፡ ከእግዚአብሄር ቃል ውጭ የሆነን ነገር ከሰማን እና ትኩረታችንን ከሰጠነው ጥርጥር ወደልባችን ይገባል፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ከሰማንና ከተቀበልን በኋላ ልባችንን ለተቃራኒ ነገር መዝጋት አለብን፡፡
ለእግዚአብሄር ቃል ልባችንን እንደከፈተን ሁሉ እንደ እግዚአብሄር ቃል ላልሆነ ሃሳብ ደግሞ ልባችንን መዝጋት አለብን፡፡ የጥርጥር ሃሳብ ወደ አእምሮዋችን ሲመጣ በፍጥነት አውጥተን መጣል አለብን፡፡ እንደ እግዚአብሄር ቃል ያልሆነ የጥርጥር ሃሳብ ለጥቂት ጊዜ እንኳን በአእምሮዋችን እንዲቆይ መፍቀድ የለብንም፡፡  
ስለ አለንበት ሁኔታ የእግዚአብሄርን ቃል ከፈለግህንና ካገኘንም በኋላ በቃሉ ላይ መቆም አለብን፡፡ ቃሉን በእምነት መናገር አለብን፡፡ ቃላችን ከእግዚአብሄ ቃል ጋር መስማማት አለበት፡፡ የምንናገረውን የእግዚአብሄ ቃል ካለጥርጥር መናገር ማለት ይገባናል፡፡
እውነት እላችኋለሁ፥ ማንም ያለው ነገር እንዲደረግለት ቢያምን በልቡ ሳይጠራጠር፥ ይህን ተራራ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ቢል ይሆንለታል። ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ፥ ይሆንላችሁማል። ማርቆስ  11፡23-24
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #መናገር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ቃል #ማሰላሰል #ማድረግ #ሁሉይቻላል #ጥርጥር #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment