Popular Posts

Tuesday, April 18, 2017

ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው

ከፈሪሳውያንም ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ፦ መምህር ሆይ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህን ምልክቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን አለው። ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ኒቆዲሞስም፦ ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው። ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም። ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው። ዮሐንስ 3፡3-6
ኢየሱስ ኒቆዲሞስ ለተባለው የህግ መምህር ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሄርን መንግስት ሊያይ አይችልም አለው፡፡
ሰው ወደዚህ ምድር ለመግባት ከእናትና ከአባቱ መወለድ አለበት፡፡ ይህ መወለድ የመጀመሪያው መወለድ ነው፡፡ ስለዚህ መወለድ መፅሃፍ ቅዱስ በዮሃንስ 1፡13 ሲናገረው ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ በማለት ወደምድር መግቢያውን መንገድ ይናገራል፡፡
ወደዚህ ምድር ለመግባት በስጋ ከእናትና ከአባታችን እንደተወልድን ሁሉ መንፈስ ወደ ሆነው በአይን ወደማይታየው ወደ እግዚአብሄር መንግስት ለመግባት ደግሞ እንዲሁ መወለድ አለብን፡፡ የእግዚአብሄር መንግስት በመንፈስ እንጂ በስጋ አይን ስለማትታይ በመካከላችን ብትሆንም ዳግመኛ ካልተወለድን ልናያት አንችልም፡፡
ፈሪሳውያንም፦ የእግዚአብሔር መንግሥት መቼ ትመጣለች ብለው ቢጠይቁት፥ መልሶ፦ የእግዚአብሔር መንግሥት በመጠባበቅ አትመጣም፤ ደግሞም፦ እንኋት በዚህ ወይም፦ እንኋት በዚያ አይሉአትም። እነሆ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናትና አላቸው። ሉቃስ 17፡20-21
ከእናትና ከአባታችን ባንወለድ ኖሮ ወደ ምድር መንግስት መግባት እንደማንችል ሁሉ መንፈስ ከሆነው ከእግዚአብሄር ካልተወለድን በስተቀር ወደ እግዚአብሄር /መንፈስ/ መንግስት መግባት አንችልም፡፡
እግዚአብሔር መንፈስ ነው፥ ዮሃንስ 4፡24
መንፈስ ከሆነው ከእግዚአብሄር የተወለደው መንፈስ እንጂ ሌላ ሊሆን አይችልም፡፡ ሰው ከእናትና ከአባቱ ካልተወለደ የምድርን መንግስት ማየት እንደማይችል ሁሉ ሰው ደግሞ መንፈስ ከሆነው ከእግዚአብሄር ካልተወለደ የመንፈስን መንግስት ሊያይ አይችልም፡፡
መጀመሪያ ከእናትና ከአባቱ የተወለደ ሰው ሁለተኛ መንፈስ ከሆነው ከእግዚአብሄር ካልተወለደ በስተቀር የእግዚአብሄርን መንግስት ሊያይ አይችልም፡፡
ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ዮሃንስ 3፡3
ከእናትና ከአባታችን የተወለድነውን የመጀመሪያውን መወለድ የስጋ መወለድ ይለዋል፡፡ ወይም ስጋችን ከስጋ እንደተወለደ ይናገራል፡፡ ከእናታችንና ከአባታችን የተወለደው ስጋችን ነው፡፡ መንፈስ ከሆነው ከእግዚአብሄር የሚወለደው ደግሞ መንፈሳችን ነው፡፡
ሰው ከእናትና ከአባት ካልተወለደ በስተቀር ወደቤተሰብ መግባት እንደማይችል ሁሉ ሰው መንፈስ ከሆነው ከእግዚአብሄር ካልተወለደ በስተቀር ወደእግዚአብሄር ቤተሰብ ውስጥ መግባት አይችልም፡፡
ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም። ዮሃንስ 1፡12-13
ስለዚህ ነው ከስጋ የተወለደ ስጋ ነው፡፡ ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው፡፡ መንፈስ ከሆነው ከእግዚአብሄር የተወለደው መንፈስ ነው፡፡ ከእግዚአብሄር የተወለደ መንፈስ እንጂ ሌላ ምንም ነገር ሊሆን አይችልም፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #በክርስቶስ #መንፈስ #የእግዚአብሄርልጅ #ስጋ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ማየት #የእግዚአብሄርመንግስት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አዲስፍጥረት #ክርስቶስ #የእግዚአብሄርቤተሰብ #ማእረግ #ስልጣን

No comments:

Post a Comment