Popular Posts

Sunday, April 16, 2017

የትንሳኤ በዓል በዓመት 365 ቀናት እንደሚከበር ያውቁ ኖሯል?

የትንሳኤ በአል በአመት አንዴ ከ365 ቀናት ውስጥ አንድ ቀን የሚከበር ከሆነ ከንቱ ነው፡፡ የትንሳኤ በአል መከበር ያለበት በህይወታችን ዘመን ሁሉ ነው፡፡ ኢየሱስ እንደሞተና እንደተነሳ በሁሉም የአመቱ ቀኖች መኖትር ይኖርብናል፡፡ ኢየሱስ የሞተበትንና የተነሳበትን አላማ በሁሉም የአመቱ ቀኖች ተጠቃሚ መሆን ይኖርብናል፡፡
ኢየሱስ ስለሃጢያታችን ሞቷል፡፡ እኛ ደግሞ 365 ቀናት ለሃጢያት ልንሞት ይገባናል፡፡
ከእንግዲህስ ወዲያ ለኃጢአት እንዳንገዛ የኃጢአት ሥጋ ይሻር ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ እናውቃለን፤ የሞተስ ከኃጢአቱ ጸድቋልና። ሮሜ 6፡6
ኢየሱስ በመሰቀል ላይ ተሰቅሎዋል እኛ ደግሞ 365 ቀናት ለአለምና ለምኞቱ መሞት ይገባናል፡፡
ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ። ገላትያ 6፡14
ኢየሱስ በሶስተኛው ቀን በድል ከሞት ተነስቷል፡፡ እኛም ለፅድቅ ህያው መሆን አለብን፡፡ ኢየሱስ በታላቅ ሃይል ከሙታን እንደተነሳ እኛም በመለኮራዊ ሃይል 365 ቀኖችን ለእግዚአብሄር መኖር ይገባናል፡፡
እንዲሁም እናንተ ደግሞ ለኃጢአት እንደ ሞታችሁ፥ ግን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ሆናችሁ ለእግዚአብሔር ሕያዋን እንደ ሆናችሁ ራሳችሁን ቁጠሩ። ሮሜ 6፡11
ካልሆነ ግን በአመት አንድ ቀን ትንሳኤን ማክበት ከንቱ ነው፡፡ በአመት አንድ ቀን ብቻ ትንሳኤን ማክበር ኢየሱስ የሞተበትን አላማ መሳት ነው፡፡
መድኃኒታችንም ከዓመፅ ሁሉ እንዲቤዠን፥ መልካሙንም ለማድረግ የሚቀናውን ገንዘቡም የሚሆነውን ሕዝብ ለራሱ እንዲያነጻ፥ ስለ እኛ ነፍሱን ሰጥቶአል። ቲቶ 2፡14
መልካም የትንሳኤ ህይወት!
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ህይወት #ትንሳኤ #ሃይል #ስልጣን #ፋሲካ #ትንሳኤ #ሞት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ  #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment