Popular Posts

Sunday, March 26, 2017

ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው

የቆምነው ከእግዚአብሄር ምህረት የተነሳ ነው፡፡
ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፤ ርኅራኄው አያልቅምና። ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ ታማኝነትህ ብዙ ነው። ሰቆቃው ኤርምያስ 3፡22-23
እግዚአብሄር ይቅር ባይ ነው ለዘላለም አይቆጣም
እግዚአብሔር መሓሪና ይቅር ባይ ነው፥ ከቍጣ የራቀ ምሕረቱም የበዛ። ሁልጊዜም አይቀሥፍም፥ ለዘላለምም አይቈጣም። መዝሙር 103፡8-9
የእግዚአብሄር ምህረት ለልጅ ልጅ ነው፡፡
እግዚአብሔር ቸር፥ ምሕረቱም ለዘላለም፥ እውነቱም ለልጅ ልጅ ነውና። መዝሙር 100፡5
የእግዚአብሄር ምህረት ለዘላለም ነው፡፡
እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና። መዝሙር 136፡1
እግዚአብሄር ስለምህረቱ ሊመሰገን ይገባዋል፡፡
ሃሌ ሉያ። ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ መዝሙር 107፡1
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሃሪ #ፀሎት #ይቅርባይ #ርኅራኄ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #የእግዚአብሄርቃል #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ምህረት #ይቅርታ #ምስጋና

No comments:

Post a Comment