Popular Posts

Saturday, March 11, 2017

የአብርሃም እምነት

እርሱም፦ ለብዙ አሕዛብ አባት አደረግሁህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ለሙታን ሕይወት በሚሰጥ የሌለውንም እንዳለ አድርጎ በሚጠራ ባመነበት በአምላክ ፊት የሁላችን አባት ነው።ዘርህ እንዲሁ ሊሆን ነው እንደ ተባለ፥ ተስፋ ባልሆነው ጊዜ የብዙ አሕዛብ አባት እንዲሆን ተስፋ ይዞ አመነ። የመቶ ዓመትም ሽማግሌ ስለ ሆነ እንደ ምውት የሆነውን የራሱን ሥጋና የሳራ ማኅፀን ምውት መሆኑን በእምነቱ ሳይደክም ተመለከተ፤ ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም። ሮሜ 4፡16-21
እግዚአብሄር ለአብርሃም በእርጅናው ወራት ልጅን እሰጥሃለሁ አለው፡፡ አብርሃምም እግዚአብሄርን አመነ፡፡ አብርሃም የእግዚአብሄርን ቃል እንዳለ ተቀበለው፡፡
እግዚአብሄር ለሙታን ህይወትን ይሰጣል፡፡ እግዚአብሄር የሌለውን እንዳለ አድርጎ ይጠራል፡፡ እግዚአብሄር ልጅን እሰጥሃለሁ ሲለው አብርሃም ለሙታን ህይወትን በሚሰጥ የሌለውን እንዳለ አድርጎ በሚጠራ በእግዚአብሄር ይህንንም ማድረግ እንደሚችል ተማመነበት፡፡
አንድም ልጅ የሌለውን አብርሃምን ዘርህ እንደ ምድር አሸዋ እንደ ሰማይ ከዋክብት ይበዛል የተባለውን ቃል አመነ፡፡ ሳራም እርሱም ምንም ቢያረጁም በተፈጥሮአዊ ተስፋ የሌለው ቢሆንም የእግዚአብሄርን ቃል ተስፋ አድርጎ አመነ፡፡ በተፈጥሮ ያጣውን ተስፋ በእግዚአብሄር ቃልኪዳን ተስፋ አገኘ፡፡
የመቶ አመት ሽማግሌ ሆኖ የእግዚአብሄርን ቃል እንጂ ሙት የሆነውን የራሱን ስጋና የሳራን ማህፀን አልተመለከተም፡፡ እንደሙት በሆነው በእርሱ ስጋና በሳራ ማህፀን ላይ አላተኮረም፡፡ ሙት ከሆነው ከራሱ ስጋና ከሳራ ማህፀን በስቲያ የእግዚአብሄርን የተስፋ ቃል ላይ አተኮረ፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ተስፋ በእምነቱ ሳይደክም ተመለከተ፡፡
እግዚአብሄር የሰጠው የተስፋ ቃል እንደሚፈፀም በመተማመን ለእግዚአብሄር ክብርን ይሰጥ ነበር፡፡ እግዚአብሄር የሰጠውን ተስፋ ሊፈፅመው እንደሚችል ተረድቶ አርፎ ነበር፡፡
አብርሃም በእምነት በረታ እንጂ ጥርጥር በህይወቱ እንዲገባ አልፈቀደለትም፡፡ አብርሃም ለእምነት እንጂ ለጥርጥር ሃሳቡን አይሰጥም ነበር፡፡
እርሱም፦ ለብዙ አሕዛብ አባት አደረግሁህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ለሙታን ሕይወት በሚሰጥ የሌለውንም እንዳለ አድርጎ በሚጠራ ባመነበት በአምላክ ፊት የሁላችን አባት ነው።ዘርህ እንዲሁ ሊሆን ነው እንደ ተባለ፥ ተስፋ ባልሆነው ጊዜ የብዙ አሕዛብ አባት እንዲሆን ተስፋ ይዞ አመነ። የመቶ ዓመትም ሽማግሌ ስለ ሆነ እንደ ምውት የሆነውን የራሱን ሥጋና የሳራ ማኅፀን ምውት መሆኑን በእምነቱ ሳይደክም ተመለከተ፤ ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም። ሮሜ 4፡16-21
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ማየት #አለማየት #ቃል #የእምነትተጋድሎ #ተስፋ #አለማመን #የእግዚአብሄርቃል #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ጥርጥር #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment