Popular Posts

Monday, January 23, 2017

የእውነተኛ ስኬት ምንጭ

ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ። ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል። እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል። መዝሙር 1፡1-3
በእግዚአብሄር ህግ ደስ የሚለው ሰው ምስጉን ነው
የእግዚአብሄር ቃል ተስፋችን ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ስኬታችን ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ህይወታችን ነው፡፡ በእግዚአብሄር ቃል ደስ የሚለው ሰው እንደሚሳካለት ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ለእግዚአብሄር ቃል እክብሮት ያለው ሰው ሊወድቅ አይችልም፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል የሚወድ ሰው እንደሚወጣና እንደሚወርስ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ብርሃን እንደሆነና የትኛውም ጨለማ ሊያሸንፈው እንደማይችል እንዲሁ የእግዚአብሄርን ቃል የያዘ ሰው ሊቋቋመው የሚችል  ከሰማይ በታች ምንም ሃይል የለም፡፡
ብርሃንም በጨለማ ይበራል፥ ጨለማም አላሸነፈውም። ዮሐንስ 1፡5
የእውነተኛ ስኬት ምንጩን ያገኘ ሰው የተመሰገነ ነው
የእውነተኛ ስኬት ምንጩ የእግዚአብሄር ቃል ስለሆነ ሰው ለስኬት የሚያስፈልገው የእግዚአብሄር ቃል ብቻ ነው፡፡ ሰው በእግዚአብሄር መልክ ስለተፈጠረ ካለ እግዚአብሄር ቃል ሙሉ ሊሆን አይችልም፡፡ ሰው በእግዚአብሄር መልክና አምሳል ስለተፈጠረ ካለ እግዚአብሄር ቃል ማሰብና ማሰላሰል እውነተኛ ስኬት ውስጥ መግባት አይችልም፡፡  
እርሱም መልሶ፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው። ማቴዎስ 4፡4
ዘላቂ ስኬት ያለው ሰው የተመሰገነ ነው
ብዙ ስኬት የሚመስሉ ወቅታዊ ነገሮች አሉ፡፡ ስኬቶች ይመጣሉ ይሄዳሉ፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ስኬት ግን ምንም የማይለውጠው ስኬት ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ስኬት ዘመን የማይሽረው ስኬት ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ስኬት በሌሎች በምንም ነገሮች የማይቀያየር ስኬት ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ስኬት ሰይጣንም ሆነ ምንም ሁኔታ የማይወሰን አስተማማኝ ስኬት ነው፡፡
የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም። ኢያሱ 1፡8
ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ። ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል። እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል። መዝሙር 1፡1-3
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ስኬት #ክንውን #ቃል #ማሰላሰል #አእምሮ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ብፅእና  #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment