Popular Posts

Friday, November 18, 2016

የገንዘብ ሚስጥር

የገንዘብን ልክ አለማወቅ በህይወት እንድንሳሳት የሚያደርግና ህይወታችንን በሙላት እንዳንደሰትበት የሚያደርግ ነገር ነው፡፡ የሰውን ብስለት የሚለካው ሰው ለገንዘብ ያለውን ስፍራ በማየት ነው፡፡ ሰው ለገንዘብ ያለውን ግምት ከተበላሸ ሌሎች ነገሮች ያለው ሁሉ ግምት ይበላሻል፡፡
ሰው ገንዘብ ማድረግ የሚችለውንና ገንዘብ ማድረግ የማይችለውን ጠንቅቆ ካልተረዳ ከገንዘብ ጋር ያለው ግንኙነት ይበላሻል፡፡ ሰው ከልክ በላይ ለገንዘብ ክብር ከሰጠና ገንዘብን በህይወቱ መጀመሪያ ካደረገ ገንዘብን ይወዳል ይባላል፡፡
ገንዘብን መውደድ ወይም ከገንዘብ ጋር ያለ የተሳሳተ ግንኙነት ወይም ለገንዘብ ያለ የተሳሳተ ግምት ከሌሎች ነገሮች ጋር ያለ ግንኙነትን ሁሉ ያዛባል፡፡ ሰው ከገንዘብ ጋር ያለው ግንኙነት ከተሳሳተ ሌላ የማይሳሳት ምንም ግንኙነት አይኖረውም፡፡
ገንዘብን መውደድ የክፋት ሁሉ ሥር ነውና፥ አንዳንዶች ይህን ሲመኙ፥ ከሃይማኖት ተሳስተው በብዙ ሥቃይ ራሳቸውን ወጉ።1ኛ ጢሞቴዎስ 6:10
ገንዘብን የሚወድ ክቡሩን ሰውን አይወድም፡፡ ገንዘብን የሚወድ ሰው እግዚአብሄርን ይጠላል፡፡ ገንዘብን የሚወድ ሰው ገንዘብን ከሰው ያስበልጣል፡፡ ገንዘብን የሚወድ ሰውን መናቅ አይከብደውም፡፡ ገንዘብን የሚወድ ሰው እግዚአብሄርን ለመውደድ አቅም ያጣል፡፡ ለገንዘብ የሚገዛ ለእግዚአብሄር መገዛት አይችልም፡፡
ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማንም የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላል ሁለተኛውንም ይወዳል፤ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንም ይንቃል፤ ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም። ማቴዎስ 6፡24
ገንዘብን የሚወድ ገንዘብን ስለማይጠግብ በህይወቱ የሚያጠግበውና የሚያረካው ምንም ነገር አይቀርለትም፡፡ ገንዘብን የሚወድ ሰው ሰው ሊያረካው አይችልም፡፡ የሰው የህይወቱ አላማና ግብ እግዚአብሄርን መውደድና እግዚአብሄርን መፈለግ ነው፡፡ ገንዘብን የሚወድ ሰው ግን የህይወቱ ብቸኛ ራእይና ግብ ገንዘብ ስለሚሆን ለእግዚአብሄር ጊዜ አይኖረውም፡፡ ገንዘብን የሚወድ ሰው በገንዘብ ፣ በሰውም ሆነ በእግዚአብሄር የመርካት እድሉን ጨርሷል፡፡
ብርን የሚወድድ ሰው ብርን አይጠግብም፤ ባለጠግነትንም የሚወድድ ትርፉን አይጠግብም፤ ይህም ደግሞ ከንቱ ነው። መክብብ 5፡10
ለተጨማሪ ፅሁፎች
#ኢየሱስ #ጌታ #ገንዘብ #ብር #ብልፅግና #ስኬት #ስምረት #መሰረታዊፍላጎት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment