Popular Posts

Thursday, November 17, 2016

ዳዊትን ገርነቱንም ሁሉ አስብ

አቤቱ፥ ዳዊትን ገርነቱንም ሁሉ አስብ፤ ለእግዚአብሔር እንደ ማለ፥ ለያዕቆብም አምላክ እንደ ተሳለ፦ በእውነት ወደ ቤቴ ድንኳን አልገባም፥ ወደ ምንጣፌም አልጋ አልወጣም፥ ለዓይኖቼም መኝታ ለሽፋሽፍቶቼም እንቅልፍ፥ ለጕንጮቼም ዕረፍትን አልሰጥም፥ ለእግዚአብሔር ስፍራ፥ ለያዕቆብ አምላክ ማደሪያ እስካገኝ ድረስ ብሎ። እነሆ፥ በኤፍራታ ሰማነው፥ በዱር ውስጥም አገኘነው። መዝሙር 132፡1-6
ከዚህም በላይ ደግሞ የአምላኬን ቤት ስለወደድሁ፥ ለመቅደሱ ካዘጋጀሁት ሁሉ ሌላ የግል ገንዘቤ የሚሆን ወርቅና ብር አለኝና ለአምላኬ ቤት ሰጥቼዋለሁ። 1ኛ ዜና 29፡3
እግዚአብሄር እንደልቤ ያለው በዘመኑ የእግዚአብሄርን ሃሳብ ካገለገለ በኋላ አንቀላፋ የተባለለት ሰው ነው-ዳዊት፡፡ ዳዊት እንደልቤ ያስባለውን ስለ እግዚአብሄር ቤት ያለውን ቅናት በሚናገረው ንግግሩና በድርጊቱ በቀላሉ ልንመለከት እንችላለን፡፡
ዳዊት ንጉስ ነው፡፡ ነገር ግን ለእግዚአብሄር ቤት ስራ የሚሆነውን ዛፍ ለመምረጥ በዱር ውስጥ ይዞር ነበር፡፡ ዳዊት የእግዚአብሄርን ስራ እስከሚሰራ አያርፍም ነበር፡፡ እጅግም ይተጋ ነበር፡፡
ዳዊት የሚያደርጋቸው ነገሮች ለቤቱ ስራ ያለውን ቅናት ያሳያል፡፡ ሲፀልይም የዳዊትን ገርነቱን መሰጠቱን ትጋቱን አስብ ይል ነበር፡፡ ገርነትና ለእግዚአብሄር ስራ ራስን መካድ እግዚአብሄር በእርግጥ የሚከፍለው ነገር ነው፡፡ እግዚአብሄር ገርነትን አይቶ አያልፈውም፡፡
ለእግዚአብሄር በነገር ሮጦ የሚበዛ እንጂ ሊከስር የሚችል ሰው የለም፡፡ በመስጠት እግዚአብሄርን አንበልጠውም፡፡ ለእግዚአብሄር በመስጠት እግዚአብሄርን አናስደነግጠውም፡፡
ዳዊት ለእግዚአብሄር ቤት ስራ የዋህ ነበር፡፡ ዳዊት በእግዚአብሄር ቤት ስራ ብልጣ ብልጥ አልነበረም፡፡ ለእግዚአብሄር ቤት ስራ የሚሰጠው በስሌት አልነበረም፡፡ ዳዊት ለጌታ በገርነትና በመሰጠት ራስን በመካድ ቆንጠጥ የሚያደርግ ስጦታን ነበር የሚያደርገው፡፡ ዳዊት ጌታን ስለሚወድ ምንም መስዋእትነት ለጌታ ብዙ አይደለም፡፡
አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ አለ። ማቴዎስ 25፡24-25
አቤቱ፥ ዳዊትን ገርነቱንም ሁሉ አስብ፤ ለእግዚአብሔር እንደ ማለ፥ ለያዕቆብም አምላክ እንደ ተሳለ፦ በእውነት ወደ ቤቴ ድንኳን አልገባም፥ ወደ ምንጣፌም አልጋ አልወጣም፥ ለዓይኖቼም መኝታ ለሽፋሽፍቶቼም እንቅልፍ፥ ለጕንጮቼም ዕረፍትን አልሰጥም፥ ለእግዚአብሔር ስፍራ፥ ለያዕቆብ አምላክ ማደሪያ እስካገኝ ድረስ ብሎ። እነሆ፥ በኤፍራታ ሰማነው፥ በዱር ውስጥም አገኘነው። መዝሙር 132፡1-6
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ገርነት #መሰጠት #የዋህ #ራስንመካድ #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment