Popular Posts

Friday, November 11, 2016

መጤ አይደለንም

ክርስትያን በተለያየ ምክኒያት ከትውልድ ሃገሩ ወጥቶ በሌላ ሃገር ይኖራል፡፡እግዚአብሄር ከአንድ ቦታ ይልቅ በሌላ ቦታ እንድናገለግለው እርሱን እያሳየን አንድንኖር ሲፈልግ በሮችን ይከፍታል፡፡
ራሳችንን ለጌታ ከሰጠንበት ጊዜ ጀምሮ እግዚአብሄር እየመራን ነው፡፡ እግዚአብሄር ተመለስ ብሎ እስካልተናገረን ድረስ በእግዚአብሄር ሃሳብ ውስጥ እንዳለን እናውቃለን፡፡ አንዳንዱ በትምህርት ምክኒያት ፣ ሌላው ለስራ ፣ ሌላው ከቀሩት የቤተሰቡ አባላት ጋር ለመኖር ፣ ሌላው ከጓደኛው ጋር ለመገናኘት የመሳሰሉት ወደ ተለያዩ አገሮች በመሄድ ይኖራል፡፡
ሰው የተለያየ ምክኒያት ይስጠው እንጂ እግዚአብሄር ፍቃዱ ካልሆነና በስተቀር የሚሰራው የእግዚአብሄር ስራ ከሌለ በስተቀር የውጭ አገር በሮች አይከፈቱም ልቡንም አያነሳሳም፡፡
ከሀገር ለመውጣት ቢፈልጉም ቢመኙም ቢፀልዩም ያልቻሉ ብዙ ሰዎችን እናውቃለን፡፡ በተቃራኒው ብዙም ሳያስቡበትና ሳይጓጉ አጋጣሚ በሚመስል መንገድና ባልተገመተ ሁኔታ አገር የለወጡ ብዙ ሰዎች ደግሞ እናውቃለን፡፡ እግዚአብሄር የሚዘጋውን የሚከፍት እንደሌለ የሚከፍተውን ደግሞ የሚዘጋ እንደሌለ መፅሃፍ ቅዱስ ያስተምረናል፡፡
በፊልድልፍያም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ፦ የዳዊት መክፈቻ ያለው፤ የሚከፍት፥ የሚዘጋም የሌለ፤ የሚዘጋ፥ የሚከፍትም የሌለ፤ ቅዱስና እውነተኛ የሆነው እርሱ እንዲህ ይላል። ራእይ 3፡7
እግዚአብሄር በውጭ አገር የፈለገውን የሚከለክል ማንም የለም፡፡ እግዚአብሄር ምድርን ሁሉ የፈጠረው ሰው እንዲኖርበትና እንዲገዛ ነው፡፡ እግዚአብሄ ፈቅዶ ልባችንን ካነሳሳና በሮችን ከፍቶ ወደሌላ አገር ከወሰደን የምንሰራው የእግዚአብሄር ስራ አለማለት ነው፡፡ ምድርና ሞላዋ የእግዚአብሄር ናት፡፡
እንዲህም አላቸው፦ ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ። ማርቆስ 16፡15
የኢየሱስ ተከታዮች በመሆናችን በትውልድ አገራችንም ይሁን ከትውልድ አገራችን ውጭ እኛ ቀድሞውንም እንግዶችና መፃተኞች ነው፡፡ እኛ ክርስቲያኖች እንግዶችና መጻተኞች የሆነው የስጋ ኑኖዋችን ጊዜያዊ አንደሆነና ከስጋ ተለይተን ከጌታ ጋር ለዘላለም እንደምንኖር ስለምናውቅ ነው፡፡ ይህች ምድር የኛ ዘላለማዊ ቤት እንዳይደለች ስላወቅንና በምድር እንደ ጊዜያዊ ተላላፊዎች ለጊዜያዊ አላማ በእንግድነት ስለምንኖር ነው፡፡
መፅሃፍ ቅዱስ ኢየሱስን ስለሚከተሉት ክርስቲያኖች የምድር ቆይታ ሲናገር ቀድሞውንም እንደ እንግዶችና እንደ መጻተኞች እንደሆነ ያስተምራል፡፡
ቀድሞም እንግዶች እንግዶች ስለሆንን ነው በአለማዊ ከንቱ ውድድር ውስጥ ገብተን የተጠራንለትን ኢየሱስን የመከተል አላማ የማንተወው፡፡ በመጨረሻ ለእርሱ እንዴት እንደኖርንለት የሚጠይቀን ጌታ እንዳለ በማወቅ ነው በምድር ላይ እንደ እንግዳና ተላላፊ የምንኖረው፡፡
ወዳጆች ሆይ፥ ነፍስን ከሚዋጋ ሥጋዊ ምኞት ትርቁ ዘንድ እንግዶችና መጻተኞች እንደ መሆናችሁ እለምናችኋለሁ፤ 1ኛ ጴጥሮስ 2፡11
እነዚህ ሁሉ አምነው ሞቱ፥ የተሰጣቸውን የተስፋ ቃል አላገኙምና፤ ዳሩ ግን ከሩቅ ሆነው አዩትና ተሳለሙት፥ በምድሪቱም እንግዶችና መጻተኞች እንዲሆኑ ታመኑ። እንዲህ የሚሉት ለእነርሱ የሚሆነውን አገር እንዲፈልጉ ያመለክታሉና። ያን የወጡበትን አገር አስበው ቢሆኑ፥ ሊመለሱ ጊዜ በሆነላቸው ነበር፤ አሁን ግን የሚበልጠውን እርሱም ሰማያዊ አገር ይናፍቃሉ። ስለዚህ እግዚአብሔር አምላካቸው ተብሎ ሊጠራ በእነርሱ አያፍርም፥ ከተማን አዘጋጅቶላቸዋልና። ዕብራውያን 11፡13-16
እኛ አገራችን በሰማይ ነውና፥ ከዚያም ደግሞ የሚመጣ መድኃኒትን እርሱንም ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን እንጠባበቃለን፤ ፊልጵስዩስ 3፡20
እኛ ቀድመን በምድር ላይ እንግዶችና መጻተኞች ነን፡፡ ቀድመን አንዴ በምድር ስንኖር እንግዶችና መጻተኞች ሆነናል፡፡ እግዚአብሄር በምድር ሁሉ ስለሚልከን ግን ከተወለድንበት ምድር ወደሌላ ምድር ስንሄድ እንግዳ አይደለንም፡፡ ሁለተኛ እንግዶችና መጻተኞች ልንሆን አንችልም፡፡
የምድር ባለቤት እግዚአብሄር ነው፡፡ ምድርና ሞላዋ የእግዚአብሄር ናት፡፡ ምድር ሁሉ የእግዚአብሄር ናት፡፡
ምድርና ሞላዋ ለእግዚአብሔር ናት: ዓለምም በእርስዋ የሚኖሩ ሁሉ፡፡ መዝሙር 24፡4
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ያድርጉ!
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ መናገር #አትፍራ #ታመን #እንግዶች #መጻተኞች

No comments:

Post a Comment