Popular Posts

Wednesday, October 5, 2016

እኔ ኤልሻዳይ ነኝ

አብራምም የዘጠና ዘጠኝ ዓመት ሰው በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር ለአብራም ተገለጠለትና፦ እኔ ኤልሻዳይ ነኝ በፊቴ ተመላለስ፥ ፍጹምም ሁን፤ ዘፍጥረት 17፡1

ሰዎች ብዙ ጊዜ እግዚአብሄር ለእነርሱ ስለሚያደርገግላቸው ነገር በጣም ሲጨነቁ ይታያል፡፡ ሰዎች ብዙ ጊዜያቸውን የሚያጠፉት ስለእግዚአብሄ ድርሻ በመጨነቅ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ ትኩረታቸው እግዚአብሄር እንዴት ቃሉን እንደሚፈፅመው በማውጣትና በማውረድ ነው፡፡እግዚአብሄርን ማንም አያስተምረውም፡፡ እንዴት እንደሚፈፅመው ያውቅበታል፡፡
እግዚአብሔር የዘላለም አምላክ፥ የምድርም ዳርቻ ፈጣሪ ነው፤ አይደክምም፥ አይታክትም፥ ማስተዋሉም አይመረመርም። ኢሳያስ 40፡28
የእግዚአብሄርን ድርሻ ለመስራት ስንሞክር የራሳችንን ድርሻ እንረሳለን፡፡ የራሳችን ድርሻ ላይ ብቻ ብናተኩር የእግዚአብሄር ፈቃድ በሙላት በህይወታችን ይፈፀማል፡፡ ወራሽ የለኝም ብሎ እግዚአብሄር ቃል ኪዳኑን እንዴት እንደሚፈፅም ላልተረዳ አብርሃም እግዚአብሄር እንዲህ አለው፡፡
እኔ ኤልሻዳይ ነኝ በፊቴ ተመላለስ፥ ፍጹምም ሁን፤
እግዚአብሔር ስለእኔ አታስብ፡፡ እኔ ሁሉን ቻይ ነኝ፡፡ ከእኔ ጋር ስትነጋገር ውስን ከሆነ ከሰው ጋር እንደምትነጋገር ማሰብ የለብህም፡፡ እኔ ሁሉን እችላለሁ እያለው ነው፡፡ ካንተ የሚጠበቀው ግን በፊቴ መመላለስ ነው፡፡ በፊቴ እንደምትኖር ኑር፡፡
በፊቴ ውጣ በፊቴ ግባ፡፡ እኔ የምታደርገውን ሁሉ ልይልህ፡፡ በምታደርገው ነገር ሁሉ ልምራህ፡፡ በዚህም ፍፁም ሁን፡፡ በዚህም ታዘዘኝ፡፡ በዚህም እኔን ስማኝ እያለ ነው ጌታ፡፡ እግዚአብሄር ስለሚፈፅምላችሁ የተስፋ ቃል አትጨነቁ፡፡
የሚያሳስባችሁ እናንተ እንዴት እንደምትኖሩለት ብቻ ይሁን ፡፡ እርሱ ቃልኪዳኑን ለመፈፀም ፍላጎቱም ችሎታውም አለው፡፡
እኔ ኤልሻዳይ ነኝ በፊቴ ተመላለስ፥ ፍጹምም ሁን፤
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ፍፁም #ተመላለስ #ኤልሻዳይ #እምነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment