Popular Posts

Saturday, October 8, 2016

ልባችሁን በመንገዳችሁ ላይ አድርጉ

ህይወት ጥንቃቄን የሚጠይቅ የስራ ሃላፊነት ነው፡፡ ይህን ሃላፊነት በሚገባ ልንወጣው እንችላለን ወይም ደግሞ ይህን ሃላፊነት በሚገባ ላንወጣው እንችላለን፡፡ ማቴዎስ 25፡14-23

ልቡን በመንገዱ ላይ ሳያደርግ ሳያስብ ፣ ሳያስተውል በዘፈቀደ የሚኖር ሰው አለ፡፡ ይህ የህይወት እውነታ ነው፡፡ አንዳንዱ እግዚአብሄርን ሲያስደስት ይኖራል አንዳንዱ ሲያሳዝነው ዘመኑ ያልፋል፡፡ እግዚአብሄር አባቱን የሚታዘዝ ልጅ አለ፡፡ እንዲሁም አባቱን የማይታዘዝ ልጅ ደግሞ አለ፡፡
ሰውም የሚያገለግለውን ልጁን እንደሚምር፥ እንዲሁ እምራቸዋለሁ። ሚልክያ 3፡17
ህይወታችንን በየጊዜው ካልመረመርንና ካልፈተሽን ግን ካላስተዋልን ማመፃችንን የምናውቀው ከእለታት አንድ ቀን ከረፈደ በኋላ ነው፡፡ ስለዚህ አስተውሉ የሚለው ጥሪ መስማት ወይም ልባችሁን በመንገዳችሁ አድርጉ የሚለው ትእዛዝ መታዘዝ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡
ኢየሱስ ስለዘሪው ምሳሌ ሲያስረዳ ቃሉ ሲዘራበት ሙሉ ፍሬ የሚያፈራው አይነት ልብን ሲናገር የሚያስተውል ብሎ ይገልፀዋል፡፡ ማስተዋል ማለት ደግሞ በቀጣይነት ማስታወስ አለመርሳት ሁሌ ማሰብ ከአእምሮ አለመጥፋት በምንወስነው ውሳኔ ሁሉ ማገናዘብ ከግምት ውስጥ መክተት ማለት ነው፡፡
በመልካም መሬት የተዘራውም ይህ ቃሉን ሰምቶ የሚያስተውል ነው፤ እርሱም ፍሬ ያፈራል አንዱም መቶ አንዱም ስድሳ አንዱም ሠላሳ ያደርጋል። ማቴዎስ 13፡23
ስለዚህ ነው በየጊዜው ከምንሰራው ከማንኛውም ነገር አለፍ ብለን ራሳችንን ማየት ያለብን፡፡ በተለይ በዚህ በፈጣንና ለማሰብ ጊዜ በማይሰጥ ዘመን ጊዜያችንን መስዋእት በማድረግ ጊዜ ወስደን የምናስብበትን ሁኔታ ማመቻቸት ይገባናል፡፡
በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ፤ 2ኛ ቆሮንቶስ 13፡5
በየጊዜው የማይፈተን ህይወት በትክክለኛ መንገድ ላይ እንዳለ ምንም ማረጋገጫ የሌለው የብክነት ህይወት ነው፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ማካፈል share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ልብ #መዳን #እምነት #ማስተዋል #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #የዘላለምህይወት #ፅናት #ማሰብ #መሪ

No comments:

Post a Comment