Popular Posts

Saturday, October 29, 2016

ለራሳቸው እንዳይኖሩ

በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ። 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡15
ክርስትና ወግን እና ስርአትን በመጠበቅ ብቻ የምንኖረው ሃይማኖት አይደለም፡፡ ክርስትና አንዳንድ ስርአቶችን በመጠበቅ ብቻ የፈለግነውን ህይወት የምንኖርበት ሃይማኖር አይደለም፡፡ ክርስትና አትንካ አትቅመስ በሚሉት ስርአቶች የሚረካ ሃይማኖት አይደለም፡፡
ኢየሱስ እኛን ለማዳን የከፈለው ወግና ስርአትን መጠበቅ አይደለም፡፡ ኢየሱስ እኛን ለማዳን የከፈለው ብርና ወርቅ አይደለም፡፡ ኢየሱስ እኛን ለማዳን የከፈለው ህይወትን ነው፡፡ ኢየሱስ እኛን ለማዳን የከፈለው ህይወቱን ነው፡፡ ኢየሱስ የሞተው እኛን ለማዳን ነው፡፡
ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል። ሮሜ 5፡8
ኢየሱስ እኛን ለማዳን ሞቶልናል፡፡ ኢየሱስ እኛን ለመታደግ ራሱን ሰጥቶዋል፡፡ ኢየሱስ እኛን ለማዳን ነው ነፍሱን ሰጥቶዋል፡፡ ኢየሱስ ነፍሱን አሳልፎ የሰጠው እኛ የፈለግነውን ኑሮ እንድንኖር አይደለም፡፡ ኢየሱስ ስለእኛ የሞተው እኛ ለእርሱ እንድንኖር ነው፡፡
ኢየሱስ የሞተው ወደፊት ለራሳችን እንዳንኖር ነው፡፡ አየሱስ ለእኛ የሞተው እኛ ለራሳችን እንድሞት ነው፡፡ ኢየሱስ ለእኛ የሞተው ለእርሱ ለሞተልን ብቻ እንድንኖር ነው፡፡
ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው። ገላትያ 2፡20
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪ #መንፈስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አገልጋይ #መንፈስቅዱስ #ምስክር #ልብ #ስለሁሉሞተ

No comments:

Post a Comment