Popular Posts

Wednesday, October 12, 2016

ወደ ልዑል እግዚአብሔር እጄን ከፍ አድርጌአለሁ

አብራምም የሰዶምን ንጉሥ አለው፦ ሰማይንና ምድርን ወደሚገዛ ወደ ልዑል እግዚአብሔር እጄን ከፍ አድርጌአለሁ፤ አንተ፦ አብራምን ባለጠጋ አደረግሁት እንዳትል፥ ብላቴኖቹ ከበሉት በቀር ከእኔ ጋር ከሄዱትም ድርሻ በቀር፥ ፈትልም ቢሆን የጫማ ማዘቢያም ቢሆን፥ ለአንተ ከሆነው ሁሉ እንዳልወስድ አውናን ኤስኮልም መምሬም እነርሱ ድርሻቸውን ይውሰዱ። ዘፍጥረት 14፡22-24

እግዚአብሄር አብርሃምን ጠራውና ከእርሱ ጋር ቃልኪዳንን ገባ፡፡
እግዚአብሔርም አብራምን አለው፦ ከአገርህ ከዘመዶችህም ከአባትህም ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ። ታላቅ ሕዝብም አደርግሃለሁ፥ እባርክሃለሁ፥ ስምህንም አከብረዋለሁ፤ ለበረከትም ሁን፤ የሚባርኩህንም እባርካለሁ፥ የሚረግሙህንም እረግማለሁ፤ የምድር ነገዶችም ሁሉ በአንተ ይባረካሉ። ዘፍጥረት 12፡1-3
አብርሃምም አምኖ እግዚአብሄርን ታዘዘ፡፡ ልጁን እስከ መስጠት ድረስ እግዚአብሄርን ተከተለው፡፡
እግዚአብሄር እንደሚባርከው አብርሃም ቅንጣት ጥርጥር አልነበረውም፡፡ አብርሃም ይጠነቀቅ የነበረው የእግዚአብሄር በረከትና የሰው በረከት በህይወቱ እንዳይቀላቀል ብቻ ነበር፡፡
ሰዎች ስጦታ ሊሰጡት ሲመጡ አመጣጣቸውን አይቶ አብራምን ባለጠጋ አደረግሁት የሚሉ አይነት ከሆነ ስጦታቸውን አይቀበልም ነበር፡፡ ምክኒያቱም አብርሃም እግዚአብሄር እንደሚባርከው ምንም ጥርጥር አልነበረውም፡፡ አብርሃም ይጠነቀቅ የነበረው የእግዚአብሄር ቃልኪዳን ሲፈፀም ከሰው ስጦታ ጋር እንዳይቀላቀልበት ነበር፡፡
የአብርሃምን የመበልፀጉን ምስጋና ሰው እንዳይወስድ ይጠነቀቅ ነበር፡፡
አብርሃምን የሚያሳስበው እግዚአብሄር ቃል ኪዳኑን ጠብቆ መባረኩ በፍፁም አልነበረም፡፡ እግዚአብሄር እንደሚባርከው ምንም ጥርጥር አልነበረውም፡፡ አብርሃምን የሚያሳስበው እግዚአብሄር ሲያበለፅገው ሰዎች ክብሩን እንዳይወስዱ ብቻ ነበር፡፡
ሰማይንና ምድርን ወደሚገዛ ወደ ልዑል እግዚአብሔር እጄን ከፍ አድርጌአለሁ፤
አብርሃም ከእግዚአብሄር ጋር የቃልኪዳን አጋር ነውና በአብርሃም መበልፀግ ማንም ምስጋናውንና ክብሩን መውሰድ የለበትም፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ማካፈል share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ልብ #መዳን #እምነት #ቃልኪዳን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #የዘላለምህይወት #አብርሃም #መንፈስ #መንፈስቅዱስ

No comments:

Post a Comment