Popular Posts

Saturday, October 29, 2016

ፍቅር ይታገሣል

ፍቅር ይታገሣል፥ ቸርነትንም ያደርጋል፤ ፍቅር አይቀናም፤ ፍቅር አይመካም፥ አይታበይም፤1ኛ ቆሮንቶስ 13፡4
የፍቅር ትርጉሙ ሌላውን ሰው በመረዳት ከዛ ሰው ጋር ራስን ማስተባበር ነው፡፡ Love is identifying self with the other in understanding.
ፍቅር አለም በራሱ ዙሪያ እንደምትዞር አያስብም፡፡ ፍቅር የራሱን ፍላጎት ብቻ አይመለከተም፡፡ ፍቅር ራስ ወዳድ አይደለም፡፡
ፍቅር ለሌላው እውቅና ይሰጣል፡፡ ፍቅር ለሌላው ፍላጎት ቦታ አለው፡፡ ፍቅር ሌላውን የሚያከብር ልብ አለው፡፡ ፍቅር የሌላው እርምጃ የሚታገስ ልብ አለው፡፡
ፍቅር ይታገሳል፡፡ ፍቅር ቻይ ነው፡፡ ፍቅር አይቸኩልም፡፡ ፍቅር አሁን ካልሆነ አይልም፡፡ ፍቅር ይቆያል፡፡ ፍቅር ይጠብቃል፡፡ ፍቅር ነገሩ በጊዜው እንደሚሆን ያምናል፡፡
ፍቅር ይታገሳል፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ፍቅር #መንፈስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ትዕግስት #መንፈስቅዱስ #ምስክር #ልብ #መሪ

No comments:

Post a Comment