Popular Posts

Friday, October 28, 2016

ሙሉ ስልጣን ተሰጥቶናል

ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፦ ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ። እንግዲህ ሂዱና . . . ማቴዎስ 28፡18

በመጀመሪያ ሰው ከሙሉ ስልጣን ጋር ተፈጥሮ ነበር፡፡

እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ እንዲህም አላቸው፦ ብዙ፥ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት፥ ግዙአትም፤ የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ግዙአቸው። ዘፍጥረት 1፡28

ሰው በሃጢያት እግዚአብሄር ላይ በማመፁ ስልጣኑን ሙሉ ለሙሉ አጣው፡፡ እግዚአብሄር የሰጠውን ስልጣን ባለመታዘዝ ምክኒያት ለሰይጣን አሳልፎ ሰጠ፡፡ ስለዚህ ነው ሰይጣን የዚህ አለም ገዢ ተብሎ የተጠቀሰው ፡፡

ለእነርሱም የእግዚአብሔር ምሳሌ የሆነ የክርስቶስ የክብሩ ወንጌል ብርሃን እንዳያበራላቸው፥ የዚህ ዓለም አምላክ የማያምኑትን አሳብ አሳወረ። 2ኛ ቆሮንቶስ 4፡4

ኢየሱስ ወደዚህ ምድር የመጣበት ዋነኛው አላማ የዲያቢሎስን ስራ ሊያፈርስና ሰው ለሰይጣን አሳልፎ የሰጠውን ስልጣን መመለስ ነው፡፡ ኢየሱስ የሰውን ስጋ ለብሶ ወደምድር የመጣውና ሰይጣንን ድል የነሳው ለራሱ ሳይሆን ለእኛ ነው፡፡ ኢየሱስ ሰይጣንን ያሸነፈው በእኛ ምትክ ሆኖ ለእኛ ነው፡፡

አለቅነትንና ሥልጣናትን ገፎ፥ ድል በመንሣት በእርሱ እያዞራቸው በግልጥ አሳያቸው። ቆላስይስ 2፡15

አሁንም ሰው ኢየሱስን እንደ አዳኝና ጌታው ሲቀበለው የልጅነት ስልጣኑ ይመለሳል፡፡

ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ ዮሃንስ 1፡12

የእግዚአብሄር ልጅ የሆነ ሰው ሁሉ ሰይጣንን መቃወም ይችላል፡፡ በሰይጣን ላይ ሙሉ ስልጣን ስላለን ስንቃወመው መሸሽ እንጂ ምንም ማድረግ አይችልም፡፡

እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤ ያዕቆብ 4፡7

ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ኢየሱስ #ጌታ #ስልጣን #ሃይል #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ሃይለኛ #ጩኽ #በረከት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment