Popular Posts

Monday, October 24, 2016

በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነው

ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና። 1ኛ ዮሐንስ 4፡4
አለም በክፉ ተይዞዋል፡፡ አለም እንዲደግፈንና እንዲያበረታታን አንጠብቅም፡፡ አለም ጎሽ እንዲለንና እንዲረዳን አንጠብቅም፡፡ አለም በቻለው አቅም ይቃወመናል፡፡ አለም በቻለው አቅም ታላቅነቱን ሊያሳየን ይሞክራል፡፡ አለም በቻለው አቅም እኛ ትንሽ እነደሆንን ሊያሳየን ይሞክራል፡፡ በአለም ያለው የሚያስፈራራ ነው፡፡ በአለም ያለው የሚንቅና ዝቅ ዝቅ የሚያደረግ ነው፡፡ በአለም ያለው በፍርሃት አስሮ ለማስቀመጥ የሚጥር ነው፡፡ ከአለም የምንጠብቀው ተግዳሮትና መቋቋምን ብቻ ነው፡፡
የአለም ስርአት ከፈቀድንለት ለእግዚአብሄ እንዳንኖር አሳስሮ ሊያስቀምጠን ነው የሚጥረው፡፡ እህህ ብለን ከሰማነው እንደጠፋን እንደማይከናወንልን ነው አለም በጩኸት የሚነግረን፡፡ አለም ከሰማንና ከተቀበልነው እግዚአብሄር በህይወታችን ያለው አላማ እንደማይፈፀም ነው የሚነግረን፡፡ ምክኒያቱም አለም በክፉ ተይዟል፡፡
ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን ዓለምም በሞላው በክፉው እንደ ተያዘ እናውቃለን። 1ኛ ዮሐንስ 5፡19
አለም ምን ያህል ደካማና ለምንም የማንበቃ እንደሆንን ሊያሳየን ነው የሚፈልገው፡፡ የአለም ስርአት እኛ ምንም እንዳይደለንና ለምንም እንደማንበቃ ሊያስፈራራን ነው የሚመጣው፡፡ አለም በክፉ የተያዘ ነው፡፡ አለም ውሸትን የተሞላ ነው፡፡ እውነት የሆነው መፅሃፍ ቅዱስ ግን በእኛ ውስጥ ስላለው ሲናገር እንዲህ ይላል፡፡
በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና። ምክኒያቱም ከእግዚአብሄር ናችሁ ፡፡ ያሸነፋችሁበት ምክኒያት በእናንተ ያለው ከአለም ካለው ታላቅ ስለሆነ ነው፡፡ በውስጣችን የሚኖረው ኢየሱስ አለምን ያሸነፈ ነው፡፡
በእኔ ሳላችሁ ሰላም እንዲሆንላችሁ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። . . . ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ። ዮሃንስ 16፡33
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #አለም #ታላቅ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ጥቂትበጥቂት #ሙሉቀን #በረከት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment