Popular Posts

Sunday, October 23, 2016

አሁንም ከእግዚአብሔር ጋር ተስማማ፥ ሰላምም ይኑርህ

አሁንም ከእርሱ ጋር ተስማማ፥ ሰላምም ይኑርህ፤ በዚያም በጎነት ታገኛለህ። ኢዮብ 22:21
እግዚአብሄር የፈጠረን ለክብሩ ነው፡፡ እግዚአብሄር አቅዶ የሰራን ከእርሱ ጋር እንድንስማማ ነው፡፡ እግዚአብሄር የፈጠረን በዋነኝነት እርሱን እንድንታዘዘው ነው፡፡
በስሜ የተጠራውን ለክብሬም የፈጠርሁትን፥ የሠራሁትንና ያደረግሁትን ሁሉ አምጣ እለዋለሁ። ኢሳይያስ 43፡7
ሰው ግን ከእርሱ ጋር ካልተስማማና ለእግዚአብሄር ካልተገዛ በህይወቱ ምንም ነገር ትክክል ሊሆን አይችልም፡፡ ሰው ከእግዚአብሄር ጋር ካልተስማማ ሁሉ ነገር ስለሚዘበራረቅና ምንም የሚሳካ ነገር ስለሌለ ሰላሙን ያጣል፡፡
ስለዚህ ምክሩ አሁንም ከእግዚአብሄር ጋር ተስማማ ነው፡፡ መጀመሪያ ሰላም ታገኛለህ፡፡ እግዚአብሄር ፀጋውን ያበዛልሃል፡፡ ከዚያም በመታዘዝህ የእግዚአብሄርን በረከት ታገኛለህ ህይወትህም ይለመልማል፡፡ ኢየሱስ በመስቀል ተሰቃየ፡፡ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ ፈቃድ ይሁን በማለት ከእግዚአብሄር ጋር ተስማማ፡፡ ጨክኖም ለእግዚአብሄር ታዘዘ፡፡
ጥቂትም ወደ ፊት እልፍ ብሎ በፊቱ ወደቀና ሲጸልይ፦ አባቴ፥ ቢቻልስ፥ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ፤ ነገር ግን አንተ እንደምትወድ ይሁን እንጂ እኔ እንደምወድ አይሁን አለ።ማቴዎስ 26፡39
አሁንም ከእርሱ ጋር ተስማማ፥ ሰላምም ይኑርህ፤ በዚያም በጎነት ታገኛለህ። ኢዮብ 22:21
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #መታዘዝ #ተስማማ #ሰላም #ስኬት ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ፀጋ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment