Popular Posts

Thursday, October 6, 2016

ምኑ ነው አዲስ?

ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል። 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡17
ስለሃጢያቱ በመስቀል ላይ ዋጋ የከፈለውን ኢየሱስን የተቀበለ ሰው ሁሉ አዲስ ፍጥረት ነው፡፡ አዲሱ ሰው እርጅናና ድካም የማያውቀው አዲስ ፍጥረት ነው፡፡ ኢየሱስን እንደ አዳኙና የህይወቱ ጌታው አድርጎ የተቀበለ ሰው አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል፡፡ ግን አዲስ የሆነው ምንድነው ?
  • ልጅነቱ አዲስ ነው፡፡ ሰው በሃጢያት እስራት እያለ የእግዚአብሄር ልጅ አልነበረም፡፡ እውነት ነው የእግዚአብሄር ፍጥረት ነው የእግዚአብሄር ልጅ ግብን አልነበረም፡፡ ሰው በአመፅ ሲኖር የዲያቢሎስ ልጅ ነው፡፡
እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና። ዮሃንስ 8፡44
ወዳጆች ሆይ፥ አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን፥ ምንም እንደምንሆን ገና አልተገለጠም። 1ኛ ዮሃንስ 3፡2
  • ወዳጅነታችን አዲስ ነው፡፡ ሰው ከእግዚአብሄር ጋር ወዳጅ አልነበረም፡፡ ሰው የእግዚአብሄር ጠላት ነበረ፡፡ አሁን ግን ሰው በክርስቶስ የእግዚአብሄር ወዳጅ መሆን ይችላል፡፡
ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ ሞት ከታረቅን፥ ይልቁንም ከታረቅን በኋላ በሕይወቱ እንድናለን፤ ሮሜ 5፡10
ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም፤ ባርያ ጌታው የሚያደርገውን አያውቅምና፤ ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ፥ ከአባቴ የሰማሁትን ሁሉ ለእናንተ አስታውቄአችኋለሁና። ዮሃንስ 15፡15
  • ህያውነታችን አዲስ ነው፡፡ ሰው ቆሞ ይሂድ እንጂ በእግዚአብሄር እይታ ሙት ነበረ፡፡ ሰው በሃጢያት ምክኒያት ለዘላለም ከእግዚአብሄ ተለይቶ ነበረ፡፡ ሰው ክርስቶስን በመቀበል እግዚአብሄር ይቀበለዋል፡፡ ለዘላለም ከእግዚአብሄር ጋር ይኖራል፡፡
በበደላችሁና በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ፤ ኤፌሶን 2፡1
ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥ ኤፌሶን 2፡5
  • የሰይጣን መጠቀሚያ ነበርን፡፡ የምንኖረው በሰይጣን ፈቃድ ነበር፡፡ አሁን ግን ከሰይጣን ግዛት ወጥተናል፡፡ እኛ ስፍራ ሰጥተነው ካልሆነ ሰይጣን በእኛ ላይ ምንም ስልዕጣን የለውም፡፡
በዚህ ዓለም እንዳለው ኑሮ፥ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ እንደ ሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው አለቃ ፈቃድ፥ በፊት ተመላለሳችሁባቸው። ኤፌሶን 2፡2
እነሆ፥ እባቡንና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ፥ በጠላትም ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችኋለሁ፥ የሚጐዳችሁም ምንም የለም። ሉቃስ 10፡19
  • ሰላማችንና መታረቃችን አዲስ ነው፡፡ የቁጣ ልጆች ነበርን፡፡ እግዚአብሄር በሃጢያታችንና በአመፃችን ደስተኛ አልነበረም፡፡ አሁን እግዚአበሄ ተቀብሎናን ኢየሱስ በመስቀል ላይ በሰራው ስራ እግዚአብሄር በእኛ ደስተኛ ነው፡፡ እግዚአብሄር ረክቷል፡፡
በእነዚህም ልጆች መካከል እኛ ሁላችን ደግሞ፥ የሥጋችንንና የልቡናችንን ፈቃድ እያደረግን፥ በሥጋችን ምኞት በፊት እንኖር ነበርን እንደ ሌሎቹም ደግሞ ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን። ኤፌሶን 2፡3
እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ሁለቱን ያዋሐደ በአዋጅ የተነገሩትንም የትእዛዛትን ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳን በሥጋው ያፈረሰ፤ ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ፥ 2ኛ ቆሮንጦስ 5፡14-15
  • ተስፋችን አምላካችን አዲስ ነው፡፡ ካለ እግዚአብሄር ካለተስፋ ነበርን፡፡ አሁን ግን አምላክ አለን፡፡ አሁን ግን ተስፋችን ሙሉ ነው፡፡
በዚያ ዘመን ከእስራኤል መንግሥት ርቃችሁ ለተስፋውም ቃል ኪዳን እንግዶች ሆናችሁ በዚህም ዓለም ተስፋን አጥታችሁ ከእግዚአብሔርም ተለይታችሁ ያለ ክርስቶስ ነበራችሁ። ኤፌሶን 2፡12 
  
መጥቶም ርቃችሁ ለነበራችሁ ለእናንተ ሰላምን፥ ቀርበው ለነበሩትም ሰላምን የምስራች ብሎ ሰበከ፤ በእርሱ ሥራ ሁላችን በአንድ መንፈስ ወደ አብ መግባት አለንና። እንግዲያስ ከእንግዲህ ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና የእግዚአብሔር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም። ኤፌሶን 2፡17-19 
ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል። 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡17
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ 
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#አዲስፍጥረት #አዲስ #መዋጀት #መዳን #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ሰላም ትግስት #ልጅ

No comments:

Post a Comment