Popular Posts

Monday, October 10, 2016

እግዚአብሔርም በጽኑ እጅ እንዲህ ተናገረኝ

እግዚአብሔርም በጽኑ እጅ እንዲህ ተናገረኝ፥ በዚህም ሕዝብ መንገድ አንዳልሄድ አስጠነቀቀኝ፥ እንዲህም አለኝ፦ ይህ ሕዝብ፦ ዱለት ነው በሚሉት ሁሉ፦ ዱለት ነው አትበሉ፤ መፈራታቸውንም አትፍሩ፥ አትደንግጡ። ኢሳይያስ 8፡11-12

ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ አትናወጡም፥ ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስ በልባችሁ ቀድሱት። 1ኛ ጴጥሮስ 3፡14-15
መቼም ቢሆን ደግሞ ሁኔታን እንድንፈራ እግዚአብሄር አይፈልግም፡፡ አይናችን ከእግዚአብሄር ላይ ተነስቶ ሁኔታ ላይ ሲሆን ከእግዚአብሄር ጋር ያለን ግንኙነት ይዛባል ፍሬያማነታችን ይቀንሳል፡፡
እኛ በክርስቶስ አምነን ከእግዚአብሄር ጋር የታረቅን ሁሉን የሚያውቅ አባት ነው ያለን፡፡ እኛ የክርስቶስ ተከታዮች ሁሉን ቻይ የሆነ አምላከ ነው ያለን፡፡ ከእኛ በላይ ሊረጋጋ የሚገባው ከእኛ በላይ ከፍርሃት በላይ ሆኖ ሊኖር የሚገባው ከእኛ በላይ ከሁኔታዎች በላይ ሆኖ ሊወጣና ሊገባ የሚገባው ሰው የለም፡፡ እንዲያውም የጌታችንን ብርሃን የምናሳየውና የምናንፀባርቀው ጨለማ ምድርን ድቅድቅ ጨለማም አሕዛብን ሲሸፍን ነው፡፡ ኢሳያስ 60፡1
ለእኛ ግን ጨለማ አይሆንም፡፡ ለእኛ ግን መጥፊያ አይደለም፡፡ ለእኛ ግን በእድል የተሞላ ዘመን ነው፡፡ ለእኛ ግን ጌታን የምናሳይበት ትልቅ እድል ነው፡፡ ለእኛ ግን ዘመን ስለማይሽረው ስለአምላካችን ሃያልነት በግልፅ የምንናገርበት ትልቅ አጋጣሚ ነው፡፡ ለእኛ ግን በአምላካችን ላይ የምንጓደድበት ዘመናችን ነው፡፡
ይህ ዘመን ለጨነቃቸው መፍትሄ አለ መንገዱ ይህ ነው ብለን የምናሳይበት ታላቅ መድረክ ነው፡፡ ስለዚህ ነው እግዚአብሄር ህዝቡን ሲያስጠነቅቅ ይህ ሕዝብ፦ ዱለት ነው በሚሉት ሁሉ፦ ዱለት ነው አትበሉ፤ ንግግራችሁ አይደባለቅ ንግግራችሁ ይለይ፡፡ ሌሎች የሚቀድሱት የሌላቸው እንደሚሉት አትበሉ፡፡ ሌሎች አምላክ የሌላችውን ቋንቋ አትጠቀሙ፡፡ ሌሎች የሚፈሩትንም አትፍሩ ፍርሃት ለእናንተ አይደለም ይላል እግዚአብሄር፡፡ መፈራት የማይገባውን እየፈራችሁ አግዚአብሄርን አታስቀኑት፡፡
መፈራታቸውንም አትፍሩ፥ አትደንግጡ። 1ኛ ጴጥሮስ 3፡14
ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስ በልባችሁ ቀድሱት።1ኛ ጴጥሮስ 3፡15
እናንተ የምታመልኩት አምላክ የተለየ መሆኑን በድርጊታችሁ አሳዩ፡፡ የእናንተ ድርሻ ጌታን ብቻ መፍራትና ለእርሱ ብቻ የተለየ ስፍራ መስጠት ነው፡፡ ሌሎችን አማልክት ከሚያመልኩ ጋር ተቀላቅላችሁ እንደ እነርሱ የሽንፈት ወሬ እያወራችሁ እርሱን ከሌሎች አማልክት ጋር አትቀላቅሉት፡፡ እግዚአብሄር በልባችሁ ብቸኛውን ስፍራ ይፈልጋል፡፡
ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ አትናወጡም፥ ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስ በልባችሁ ቀድሱት። 1ኛ ጴጥሮስ 3፡14-15
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ማካፈል share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ኢየሱስ #ጌታ #ቀድሱት #መዳን #እምነት #አትፍሩ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #የዘላለምህይወት #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment