Popular Posts

Thursday, September 15, 2016

አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥

ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና። ማቴዎስ 5፡8
ስለዚህ ነው እግዚአብሄር እንደልቤ ያለው ዳዊት ይህንን ፀሎት የሚፀልየው፡፡ ልባችንን ሊያቆሽሽ የሚመጣ ነገር ባለበት የፃም የልብ ጩኸት የልብ ንፅህና ነው፡፡
አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ። መዝሙር 51፡10
ልበ ንጹሖች እግዚአብሄርን ያዩታል፡፡ በስራቸው እግዚአብሔርን ያዩታል በህይወታቸው የእግዚአብሄር ክንድ ያያሉ፡፡ በኑሮዋቸው የእግዚአብሔርን ሃይል ያያሉ፡፡ በአካሄዳቸው የእግዚአብሔርን ክንድ ያዩታል፡፡ በዘመናቸው እግዚአብሔርን በስራ ላይ ያዩታል፡፡ ልበ ንጹሖች እግዚአብሔር ሲዋጋላቸው ያዩታል፡፡
እግዚአብሔር ንፁህና ቅዱስ ነው፡፡ ካለቅድስና እግዚአብሄርን ማየት አይቻልም፡፡ እግዚአብሄር ይኖራል ይሰራልም፡፡
እግዚአብሄርን በህይወታችን ለማየት ግን የልብ ንፅህናን ይጠይቃል፡፡ የልብ ንፅህና ምንድነው? የልብ ንፅህና ከምኞት መንፃት ነው፡፡ ሰዎች በምኞት ልባቸው ቆሽሾ እግዚአብሔን ማየት በፍፁም አይችሉ፡፡
  • ከጥላቻ የነፃ ልብ
ሰዎች እንደ እነርሱ እግዚአብሄር የፈጠረውን ሰው ሲጠሉ እግዚአብሄር ሲሰራ ማየት ይሳናቸዋል፡፡
ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፥ እግዚአብሔር ፍቅር ነውና። እግዚአብሔር ፍቅር ነው፥ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል። 1ኛ ዮሐንስ 4፡8፣16
  • ከራስ ወዳድነት የነፃ ልብ
ሰዎች በራስ ወዳድነት ሲመላለሱ የእግዚአብሄር መኖርም ይሁን የእግዚአብሄር ስራ ይጨልምባቸዋል፡፡
በእናንተ ዘንድ ጦርና ጠብ ከወዴት ይመጣሉ? በብልቶቻችሁ ውስጥ ከሚዋጉ ከእነዚህ ከምቾቶቻችሁ አይደሉምን? ትመኛላችሁ ለእናንተም አይሆንም፤ ትገድላላችሁ በብርቱም ትፈልጋላችሁ፥ ልታገኙም አትችሉም፤ ትጣላላችሁ ትዋጉማላችሁ ነገር ግን አትለምኑምና ለእናንተ አይሆንም፤ ትለምናላችሁ፥ በምቾቶቻችሁም ትከፍሉ ዘንድ በክፉ ትለምናላችሁና አትቀበሉም። ያዕቆብ 4፡1-3
  • ከክፋትና ከቅናት የነፃ ልብ
በሰው ላይ ክፉ በማድረግ ከመርካት ልባችንን ልናጠራ ይገባናል፡፡ የሰው ውድቀትና አለመከናወን የሚያስደስተን ከሆንን እግዚአብሄርን ልናየው አንችልም፡፡
እናንተ ኃጢአተኞች፥ እጆቻችሁን አንጹ፤ ያዕቆብ 4፡8
  • ከስስት የነፃ ልብ ከስስት ነፃ መሆን፡፡ ያለኝ ይበቃኛል አለማለት፡፡ እግዚአብሄር ከሚባርከን ከመሰረታዊ ፍላጎት በላይ አለመመኘት፡፡
ጌታም እንዲህ አለው፦ አሁን እናንተ ፈሪሳውያን የጽዋውንና የወጭቱን ውጭ ታጠራላችሁ፥ ውስጣችሁ ግን ቅሚያና ክፋት ሞልቶበታል፡፡ ሉቃስ 11፡39
  • በሁለት ሃሳብ የማይወላውል ልብ እግዚአብሄርን የመጀመሪያ ማድረግ፡፡ እግዚአብሄርን ባጣ ቆየኝ አለማድረግ፡፡ በእግዚአብሄር ማመን፡፡ በእግዚአብሄር ብቻ መርካት፡፡ እግዚአብሄርን አለመጠራጠር፡፡
ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ፥ ልባችሁን አጥሩ። ያዕቆብ 4፡8
ልብን የሚያጠራው ብቸኛ መፍትሄ የእግዚአብሄን ቃል ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል የእግዚአብሄርን ቃል በተረዳንና በታዘዝነው መጠን ልባችንን ያነፃዋል፡፡ ልባችን በነፃ መጠን አግዚአብሄርን በአብሮነቱ እናየዋለን፡፡
እናንተ ስለ ነገርኋችሁ ቃል አሁን ንጹሐን ናችሁ፤ ዮሐንስ 15፡3
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#እግዚአብሔር #አምላክ #ፍቅር #እምነት #ልብ #ቃል #እረፍት #አምልኮ #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment