Popular Posts

Sunday, September 11, 2016

ቃል ቃል ቃል



ቃል ታላቅ የእግዚአብሄር ስጦታ ነው፡፡ የሰውን የልቡን ሃሳብ የምንረዳው በቃል ብቻ ነው፡፡
ምክር በሰው ልብ እንደ ጠሊቅ ውኃ ነው፤ አእምሮ ያለው ሰው ግን ይቀዳዋል። ምሳሌ 20፡5
ሰዎች ለሁልጊዜ አብረው በጋብቻ ለመኖር የሚሰጣጡት አንድ ነገር ቃል ነው፡፡
ቃል በጣም ሃያል መሳሪያ እንደመሆኑ መጠን በጣም ጥንቃቄ የሚፈልግ በውስጡ ሊያጠፋም ህይወት ሊሰጥም የሚችል እምቅ ጉልበት ያለው ነገር ነው፡፡
እንዲያውም ቃላችን የህይወታችንን ሁኔታ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ የህይወት ደረጃችን ነፀብራቅ ነው፡፡
ሁላችን በብዙ ነገር እንሰናከላለንና፤ በቃል የማይሰናከል ማንም ቢኖር እርሱ ሥጋውን ሁሉ ደግሞ ሊገታ የሚችል ፍጹም ሰው ነው። ያዕቆብ 3፡2
ስለቃል አጠቃቀም መፅሃፍ ቅዱሳዊ ምክሮች
  • ቃልህ ጥቂት ይሁን
ቃላትን ከመናገራችን በፊት እራሳችን መቅመስ አለብን፡፡ ሰው በአንድ ጊዜ ጥቂት ቃላትን ብቻ ነው ቀምሶ መናገር የሚችለው፡፡ ብዙ ቃላትን ከተናገረ አጣጥሞ ቀምሶ ፈትሾ የመናገር ችሎታው እየቀነሰ ስለሚሄድ ይስታል፡፡
በቃል ብዛት ውስጥ ኃጢአት ሳይኖር አይቀርም፤ ከንፈሩን የሚገታ ግን አስተዋይ ነው። ምሳሌ 10፡19
  • ቃሎችህ ቀላል ይሁኑ
የቃል አላማ ሃሳብን መለዋወጫ በመሆኑ ቃልህ ሁለትና ሶስት ትርጉም አይኑረው፡፡ ግልፅ ሁን፡፡ ቃሎችህ አንድ ትርጉንም ብቻ ይኑራቸው፡፡ በቃሎችህ ደግሞ ለማሳመን በጣም አትጣር፡፡ ቃሎችህ ራሳቸው ያሳምኑ፡፡ እንዲሁም በቃሎች ተማመንባቸው፡፡ ቃሎችህን ለመግባቢያ እንጂ በመሃላና በቃል ብዛት ሰዎችን አላግባብ ለመቆጣጠር አትጠቀምባቸው፡፡
ነገር ግን ቃላችሁ አዎን አዎን ወይም አይደለም አይደለም ይሁን፤ ከነዚህም የወጣ ከክፉው ነው። ማቴዎስ 5፡37
  • በወሳኝ ጊዜ ቃልን የሚሰጥህና እግዚአብሄር ነው
አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ ማቴዎስ 10፡19
  • ቃል ከመናገርህ በፊት ስማ
ሳይሰማ ነገርን በሚመልስ ስንፍናና እፍረት ይሆንበታል። ምሳሌ 18፡13
በቃሉ የሚቸኵለውን ሰው ብታይ፥ ከእርሱ ይልቅ ለሰነፍ ተስፋ አለው። ምሳሌ 29፡20
  • ቃልህ ፀጋን የሚመግብ እንደሆነ አውቀህ ሌላ አፍራሽ ነገር እንዳይሸከም ተጠንቀቅ
ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ።
ኤፌሶን 4፡29
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

No comments:

Post a Comment