Popular Posts

Friday, September 30, 2016

አስተማሪ መንፈስ ቅዱስ

ኢየሱስ በምድር በነበረበት ጊዜ ደቀመዛሙርቱን ያስተምራቸው ይመራቸው ነበር ፡፡ ኢየሱስ የመሄጃው ጊዜ ሲደርስ ደቀመዛሙርቱን እንዲህ አላቸው፡፡ ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፡፡

ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ። ዮሐንስ 14፡15-16

ኢየሱስ ሲመራቸውና ሲያፅናናቸው ለነበሩት ደቀመዛሙርት እኔ አብን እለምናለሁ ከእናንተ ጋር የሚኖር ሌላ አፅናኝ ይሰጣችኋል አላቸው፡፡

ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤ ዮሐንስ 14፡15

የተሰጠን መንፈስ ቅዱስ አንዳንድ ጊዜ በእኛ ላይ የሚያርፍ ሳይሆን በእኛ ውስጥ በመኖር የሚመራንና የሚያፅናናን የሚረዳን የሚመራን የሚደግፈን የሚያስተምረን ጠበቃ የሚቆምልን መንፈስ ነው፡፡

እርሱም ዓለም የማያየውና የማያውቀው ስለ ሆነ ሊቀበለው የማይቻለው የእውነት መንፈስ ነው፤ ነገር ግን ከእናንተ ዘንድ ስለሚኖር በውሥጣችሁም ስለሚሆን እናንተ ታውቃላችሁ።ዮሐንስ 14፡17

ይህን መንፈስ አለም ስለማያየው አይቀበለውም እኛ ግን በውስጣችን ስለሞኖርና ስለሚመራን ስለሚናገረን ስለሚያስተምረን እናውቀዋለን፡፡

አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል። ዮሐንስ 14፡16

እናንተም ከቅዱሱ ቅባት ተቀብላችኋል፥ ሁሉንም ታውቃላችሁ። እናንተስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ ይኖራል፥ ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም፤ ነገር ግን የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉ እንደሚያስተምራችሁ፥ እውነተኛም እንደ ሆነ ውሸትም እንዳልሆነ፥ እናንተንም እንዳስተማራችሁ፥ በእርሱ ኑሩ። 1ኛ ዮሐንስ 2፡20፣27

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes


#ኢየሱስ #መንፈስቅዱስ #አፅናኝ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #ቅባት #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መውደድ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

የሰው ፍቅር

በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ሆኜአለሁ። ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ። ድሆችንም ልመግብ ያለኝን ሁሉ ባካፍል፥ ሥጋዬንም ለእሳት መቃጠል አሳልፌ ብሰጥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም። 1 ቆሮንቶስ 131

ሰው የሚያከብረውም ሆነ የሚያዋርደው ፍቅር ነው፡፡ ፍቅር ያለው ሰው የከበረ ሰው ነው፡፡ ፍቅር የሌለው ሰው ደግሞ የተዋረደ ነው፡፡

ሰው የተሰራው ለፍቅር ነው፡፡ ሰው የተሰራበት አላማ ከጎደለው ባዶ ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው በመጀመሪያ እግዚአብሄርን እንዲወድ እንዲሁም ሰውን እንዲወድ ነው ፡፡

አንተም በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም አሳብህ በፍጹምም ኃይልህ ጌታ አምላክህን ውደድ የምትል ናት። ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። ሁለተኛይቱም፦ ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የምትል እርስዋን የምትመስል ይህች ናት። ከእነዚህ የምትበልጥ ሌላ ትእዛዝ የለችም። ማርቆስ 12፡30-31

ሰውን የሚያከብረው የፍቅር ድርጊት ነው፡፡ ሰው ምንም ችሎታ ቢኖረው በፍቅር ልብ ካላደረገው ምንም አይጠቅመውም፡፡ ሰው ለእግዚአብሄርም ሆነ ለሰው ምንም ስጦታ ቢሰጥ ከፍቅር ልብ የመነጨ ስጦታ ካልሆነ ከንቱ ነው፡፡

በፍቅር ያልሆነ የሰው ተሰጥኦ ከንቱ ነው፡፡ ሰው ታላቅ የመናገር ስጦታ ቢኖረው እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽልና እንደሚጮኽ ናስ ትርጉም የሌለው ረባሽ ነው፡፡  

ሰው ፍቅር ከሌለው ለማንም አይጠቅምም፡፡ ፍቅር የሌለው ሰው ለራሱም ምንም አይጠቅመውም፡፡

ሰውን የሚያከብረው ፍቅር ስለሆነ ሰው በአለም ላይ አለ የሚባለው እውቀት ቢኖረው ፍቅር ግን ከሌለው ከንቱ ነው፡፡
የሰውን መስዋዕትነት የሚያከብረው ከፍቅር ልብ መምጣቱ ነው፡፡ ሰው ድሆችን ለመመገብ ታላቅ መስዋዕትነት ቢከፍል ከፍቅር ልብ የመነጨ ግን ካልሆነ ዋጋ የለውም፡፡

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes


#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #ፍቅር #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መውደድ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Thursday, September 29, 2016

እምነት አሁን ነው

ስለእምነት አስፈላጊነት ተናግረን አናበቃም፡፡ ምክኒያቱም ምንም ምንም ብናደርግ የምናደርገው ሁሉ በእምነት መሆን አለበት፡፡ ያለእምነት እግዚአብሄርን ደስ ማሰኘት አይቻልም፡፡ ከእግዚአብሄር ጋር የተሳካ ግንኙነት እንዲኖረን እምነት ወሳኝ ነው፡፡

ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና። ዕብራውያን 11፡6

እምነትን ደግሞ የምንለማመደው አሁን ነው፡፡

እምነት ረስተን ረስተን አስቸጋሪ ነገር ሲመጣ የምንመዘው መጠባበቂያ መሳሪያ አይደለም፡፡ እምነት በቀን ተቀን ህይወታችን የምንለማመደውና የምናዳብረው ነገር ነው፡፡

በሰውነት እንቅስቃሴ ልምምድ ሰውነታችንን እንደምናስለምደው ሁሉ ራስን ለመንፈሳዊነት ነገር ማስለመድ ጊዜንና የሚጠይቅ ነገር ነው፡፡ ማስለመድ የአንድ ቀን ስራ አይደለም፡፡ ይበልጥ ቶሎ ቶሎ እንደልምድ ካደረግነውና የህይወት ዘይቤያችን ከሆነ ይበልጥ ለከባድም ነገር ለመጠቀም እየቀለለ ይሄዳል፡፡

መፅሃፍ ቅዱስ ፈተና ሳይመጣ በፊት አስቀድመን ራሳችንን  ለፈተና በፀሎት መገንባት እንዳለብን ይናገራል፡፡

ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው። ማቴዎስ 26፡41

በህይወትም በመጀመሪያ በወጣትነታችን እግዚአብሄርን እንድንፈራና ህይወታችንን በእግዚአብሄር ሃሳብ እንድንገነባ መፅሃፍ ያስተምራል፡፡

የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጕብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ፤ ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ፤መክብብ 12፡1

መፅሃፍ በክርስትና አዲስ የተወለዱ ህፃናት ለስጋና ለጠንካራ ምግብ ራሳቸውን ለማዳበር በታማኝነት ለወተት ታማኝ መሆን እንዳለባቸው ያስተምራል፡፡  

ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ። 1ኛ ጴጥሮስ 2፡2-3

እንዲሁም እምነት የምንለማመደው ከምናውቀው ከትንሹ ነገር ነው፡፡ በተረዳነው ከእግዚአብሄር ቃል የእምነትን እርምጃ መውሰድ እንጀምር፡፡ ይህ ቀላል ነገር ነው ከምንለው ጀምረን አግዚአብሄርን እንታዘዝ፡፡

ይህ የዛሬ ቀላል የእምነት እርምጃ ለነገው ከባዱ የእምነት እርምጃ መንፈሳዊ ጡንቻችንን ያሳድገዋል፡፡

  ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ያድርጉ!



#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

እግዚአብሄር ሲመራ

እግዚአብሄር ለህዝቡ መናገር ህዝቡን መምራት ይወደል፡፡ እግዚአብሄር የሚናገረው ግን ብዙ ጊዜ እንደምንጠብቀው አይደለም፡፡ ሰዎችም እግዚአብሄር ተናገረኝ ሲሉ የሚመስለን በሚታይና ግልፅ በሆነ በእንቅስቃሴ በተደገፈ ሁኔታ እግዚአብሄር የሚናገር ነው፡፡
እውነት ነው እግዚአብሄር ሁሌ ለህዝቡ መናገር ስለሚወድ በእንደዚህ አይነት መልኩም ጭምር አንዳንዴ ይናገራል፡፡ በአብዛኛው ግን እግዚአብሄር እንደዚያ በደመናና በእሳት በውጫዊ ምልክት አይናገርም፡፡
ታዲያ እግዚአብሄር ለህዝቡ ሁል ጊዜ የሚናገር ከሆነና አብዛኛውን ጊዜ ደግሞ በግልፅና በሚታይ መልኩ ካልተናገረ እግዚአብሄር እንዴት ነው ብለን ልንጠይቅ እንችላለን፡፡
እግዚአብሄር አብዛኛውን ጊዜ የሚናገረን በልባችን ነው፡፡ ይህ በልባችን በዝምታ የምንሰማው ድምፅ በጣም ዝቅተኛ ከመሆኑ የተነሳ በልባችን ውስጥ ፈልገን ማግኘት ያለብን እኛው ራሳችን ነን፡፡
ይህን ድምፅ በልባችን ፈልገን ለማግኘት በራችንን መዝጋትና አእምሮዋችንንና ሌሎችን ድምፆች ሁሉ ዝም ማሰኘት ሊጠበቅብን ይችላል፡፡
ይህ ድምፅ በልባችን ሁሌ ያለ ሲሆን መጥቶ የሚሄድ አይነት ለተወሰነ ጊዜ ብቻ የሚሰማ ድንገተኛ ድምፅ አይደለም፡፡ ለምሳሌ ስለአንድ ነገር ስናስብ የእግዚአብሄር ፈቃድ ከሆነ የደስታና የምቾት ስሜትን የሚሰጠን ወይም ደግሞ የእግዚአብሄር ሃሳብ ካልሆነ የመኮስኮስ ፣ የመቆርቆርና ያለመመቸት ስሜትን በመስጠት የሚመራን ድምፅ ነው፡፡
በአንድ አካልም የተጠራችሁለት ደግሞ የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይግዛ፤ ቆላስይስ 3፡15
ይህ በልባችን ውስጥ ፈልገን የምናገኘው ድምፅ ስለአንድ ነገር ስናስብ የእግዚአብሄርን የፈገግታ ፊትንና የእግዚአብሄርን የመኮሳተር ፊቱን በልባችን ፈልገን የምንለይበት ምሪት ነው፡፡
እግዚአብሔር አምላክ የሚናገረውን እሰማለሁ፤ ሰላምን ለሕዝቡና ለቅዱሳኑ ልባቸውንም ወደ እርሱ ለሚመልሱ ይናገራልና። መዝሙር 85፡8
ብዙ ጊዜ የእግዚአብሄርን ፈቃድ ለማወቅና ምሪቱን ለመከተል የምፈልገው በአእምሮዋችን ነው፡፡ እግዚአብሄር ግን የሚመራን በልባችን ነው፡፡ ስለአንድ ውሳኔ ስለሚያስፈልገው ነገር ስናስብ በልባችን ሰላምን ከሰጠን በአእምሮዋችን እንኳን ረብሻ ቢኖር መከተል ያለብን የልባችንን ምሪት ነው፡፡
ስለዚህ፥ እነሆ፥ አባብላታለሁ፥ ወደ ምድረ በዳም አመጣታለሁ፥ ለልብዋም እናገራለሁ። ሆሴዕ 2፡16
እግዚአብሄር ሁሌ ይናገራል፡፡ የእግዚአብሄርን ድምፅ ለመስማት ግን በጌታ ፊት በፀሎት ጊዜ መውሰድ ይጠይቃል፡፡ የእግዚአብሄርን ድምፅ ለመስማት በቃሉ ከባቢ ውስጥ መኖር ይጠይቃል፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ያድርጉ!
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Tuesday, September 27, 2016

ጌታ ሆይ እኔን ለምን?

አንዳንድ ጊዜ በጣም አስቸጋሪ ነገር ውስጥ ስንገባ "ጌታ ሆይ እኔን ለምን?" እንላለን፡፡ አንዳንዴ ጌታ ለዚህ አሳልፎ አይሰጠኝም ብለን የገመትነው ሳይሆንና በዚያ ነገር ውስጥ ስናልፍ "ጌታሆይ ለምን?" እንላለን፡፡ አንዳንዴ ያሰብነው ሳይሆን ያላሰብነው ደግሞ ሲሆን አውጥተን አውርደን ምክኒያቱን መረዳት ሲያቀተን "ጌታ ሆይ ግን ለምን?" እንላለን፡፡ 
ከእግዚአብሄር ጋር የኖሩ ሰዎች ሁሉ እግዚአብሄር ባሳለፋቸው ጎዳና ሁሉም "ግን ለምን?" ብለዋል፡፡ በአንፃሩ ከእኛ ሙሉ መታመን የሚጠብቀው እግዚአብሄር "ጌታ ሆይ እኔን ለምን?" የሚለውን ጥያቄ ሁልጊዜ አይመልስም፡፡ 
ኢዮብ የራሱን ንፅህና ተመልክቶ ተማምኖዋል፡፡ የሚያልፍበት ሁኔታ ደግሞ በጥንቃቄ ለጌታ ለሚኖር ሰው እንደማይገባ አሰበ፡፡ እግዚአብሄርን ፊት ለፊት ባገኘው በክርክር እረታው ነበር ብሎ እስከ መናገር ደርሶዋል፡፡ 
እግዚአብሄርን መከተል እንደ ጥቁርና ነጭ ሁሉንም ነገር ብጥር አድርገን አውቀነው የምንከተለው ሳይሆን ባወቅነው እውቀት እየኖርን ባልተረዳነው ነገር ደግሞ በእግአዚአብሄር ላይ እየተደገፍን የምንኖረው ኑሮ ነው፡፡ እግዚአብሄር በህይወታችን የሚሰራውመን ስራ ሁሉ ምክኒያቱን ለመረዳት እንደ እግዚአብሄር ሁሉን አዋቂ መሆን አለብን፡፡ ሁሉንም እንደማናውቅ በመረዳት እርፍ ማለት ትህትና ነው፡፡ 
ከእግዚአብሄር ጋር የኖሩ ሰዎች ሁሉ እግዚአብሄርን ተረድተውት ጨርሰው አይደለም፡፡ የተገለጠላቸው እውነት ይበቃል ብለው ባልተረዱት ነገር በእግዚአብሄር ላይ ተደግፈው ነው፡፡ እግዚአብሄርን የተረዱት በትህትና እንዲህ ይላሉ፡፡ 
ምሥጢሩ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ነው፤ የተገለጠው ግን የዚህን ሕግ ቃሎች ሁሉ እናደርግ ዘንድ ለእኛ ለዘላለምም ለልጆቻችን ነው። ዘዳግም 29፡29 
እግዚአብሄር ለምን እኔን ግን የሚል ተመሳሳይ ጥያቄ ለነበረው ለኢዮብ በቀጥታ አይደለም የመለሰው፡፡ አነጋገርህ ስራዬን ሁሉ ልቅም አድርገንህ የምትረዳ ነው የምትመስለው ነገር ግን ፍጥረትን ስፈጥር የት ነበርክ ነው ያለው፡፡ ሁሉን እንደሚያውቅ ነው የምትናገረው ምድርን ስሰራ አንተ የት ነበርክ በማለት ነበር እግዚአብሄር የኢዮብን ጥያቄ በጥያቄ የመለሰው፡፡ ግን እኔን ለምን ለሚለው ሰው እግዚአብሄር ዛሬም ይናገራል፡፡ 
እግዚአብሄር እንዲህ ይላል ሁሉንም ስላማታውቅ በእኔ ላይ ብቻ ተደገፍብኝ፡፡ ሁሉንም ዘርዝረህ ለማወቅ መሞከር ትእቢት ነው፡፡ ስለዚህ ትህትናህን ጠብቅ እመነኝ ይላል እግዚአብሄር፡፡
ያቆብም እግዚአብሄር የሚሰራውን ነገር ስላልተረዳ እግዚአብሄር የመለሰውን ለራሳችን እንስማ፡፡ 
ያዕቆብ ሆይ፥ እስራኤልም ሆይ፦ መንገዴ ከእግዚአብሔር ተሰውራለች ፍርዴም ከአምላኬ አልፋለች ለምን ትላለህ? ለምንስ እንዲህ ትናገራለህ? አላወቅህምን? አልሰማህምን? እግዚአብሔር የዘላለም አምላክ፥ የምድርም ዳርቻ ፈጣሪ ነው፤ አይደክምም፥ አይታክትም፥ ማስተዋሉም አይመረመርም። ኢሳያስ 40፡27-28 
መፍትሄው "ለምን እኔን?" የሚለውን የማይመለስ ጥያቄ ከመጠየቅ ይልቅ ሃይል የሚሰጥህ በእኔ ላይ መደገፍ ነው ይላል እግዚአብሄር፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ማድረግ የምትችለው ብቸኛ መፍትሄ በእኔ መደገፍ ነው ይላል እግዚአብሄር፡፡ የሚሆነውን ሁሉ አልረዳም ትላለህ፡፡ ሁሉን እንደማታውቅ እኔም አውቃለሁ፡፡ ሁሉንም እንድትረዳም አልጠብቅም ይላል እግዚአብሄር፡፡ ሁሉም በማውቀው በእኔ ግን እንድትደገፍ እጠብቃለሁ ይላል እግዚአብሄር፡፡ ያንተ ድርሻ ሁሉንም ማወቅ ሳይሆን በማታውቀው በእኔ መታመን ነው ይላል እግዚአብሄር፡፡ 
ለደካማ ኃይልን ይሰጣል፥ ጕልበት ለሌለውም ብርታትን ይጨምራል። ብላቴኖች ይደክማሉ ይታክቱማል፥ ጐበዛዝቱም ፈጽሞ ይወድቃሉ፤ እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም፤ ይሄዳሉ፥ አይደክሙም። ኢሳያስ 40፡29-31 
ይህንን ፅሁፍ ሼር ማድረግ ቢወዱ 
#መታመን #እምነት #መደገፍ #ልብ #ቃል #ምስጉን #ሃሳብ #ማሰላሰል #ወንጌል #ደቀመዝሙር #ኢየሱስ #ጌታ #መዳን #አማርኛ #ኢትዮጲያ #አቢይዋቁማ #ፌስቡክ #አዋጅ

Thursday, September 22, 2016

God is a Respecter of Hearts

Then Peter opened his mouth, and said, Of a truth I perceive that God is no respecter of persons: Acts 10:34

God isn’t a respecter of persons. People are impressed by others riches, beauty, might or wisdom. God isn’t the respecter of persons.

That doesn’t mean that God doesn’t have any standard to evaluate us with. God is a god of standards. But his standard isn’t human standard. But he still has standards to weigh up us with.

God isn’t a respecter of persons. He is definitely a respecter of the heart. God is a respecter of the heart position.

People look others height or look. But God doesn’t look ones height or look. But that doesn’t mean that god doesn’t judge at all or he doesn’t have any standard he evaluates us with.

But the Lord said to Samuel, “Do not consider his appearance or his height, for I have rejected him. The Lord does not look at the things people look at. People look at the outward appearance, but the Lord looks at the heart.” 1 Samuel 16:7

The Lord is looking for the right heart to strengthen the person of good heart.

For the eyes of the LORD range throughout the earth to strengthen those whose hearts are fully committed to him. 2 Chronicles 16:9

God doesn’t show favoritism according to our race Jew or Gentile. God doesn’t have a favorite race. But He definitely has a favorite heart.

For God does not show favoritism. Romans 2:11

People value the beauty of the skin. But God values the heart beauty.

Rather, it should be that of your inner self, the unfading beauty of a gentle and quiet spirit, which is of great worth in God’s sight. 1 Peter 3:4

That is why above all we have to guard our heart diligently to be in the position of God’s help in the time of need.  

Above all else, guard your heart, for everything you do flows from it. Proverbs 4:23

For More Articles https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#value #respecter #heart #relationship #personal #knowledge #son #daughter #grace #salvation #church #testimony #rejoice #preaching #Bible #theword #Abiydinsa #scriptures #abiywakumadinsa


God is a Respecter of Hearts

Then Peter opened his mouth, and said, Of a truth I perceive that God is no respecter of persons: Acts 10:34

God isn’t a respecter of persons. People are impressed by others riches, beauty, might or wisdom. God isn’t the respecter of persons.

That doesn’t mean that God doesn’t have any standard to evaluate us with. God is a god of standards. But his standard isn’t human standard. But he still has standards to weigh up us with.

God isn’t a respecter of persons. He is definitely a respecter of the heart. God is a respecter of the heart position.

People look others height or look. But God doesn’t look ones height or look. But that doesn’t mean that god doesn’t judge at all or he doesn’t have any standard he evaluates us with.

But the Lord said to Samuel, “Do not consider his appearance or his height, for I have rejected him. The Lord does not look at the things people look at. People look at the outward appearance, but the Lord looks at the heart.” 1 Samuel 16:7

The Lord is looking for the right heart to strengthen the person of good heart.

For the eyes of the LORD range throughout the earth to strengthen those whose hearts are fully committed to him. 2 Chronicles 16:9

God doesn’t show favoritism according to our race Jew or Gentile. God doesn’t have a favorite race. But He definitely has a favorite heart.

For God does not show favoritism. Romans 2:11

People value the beauty of the skin. But God values the heart beauty.

Rather, it should be that of your inner self, the unfading beauty of a gentle and quiet spirit, which is of great worth in God’s sight. 1 Peter 3:4

That is why above all we have to guard our heart diligently to be in the position of God’s help in the time of need.  

Above all else, guard your heart, for everything you do flows from it. Proverbs 4:23


#value #respecter #heart #relationship #personal #knowledge #son #daughter #grace #salvation #church #testimony #rejoice #preaching #Bible #theword #Abiydinsa #scriptures #abiywakumadinsa


Wednesday, September 21, 2016

ከሐዲ ልብ

ንድን ሰው አይታችሁዋል፡፡ እግዚአብሄርን ሲያመልክ የነበረ ሰው ፣ ጌታን አገልግሎ የማይጠግብ የነበረ ሰው ፣ እግዚአብሄርን በቀላሉ ያምን የነበረ ሰው ነገር ግን ሁሉም ነገር ጠፍቶበት እግዚአብሄርን ለቀላል ነገር ማመን ሲያቅተው ፣ የእግዚአብሄርን ሃይል ሲክድና ባለማመን ሲሞላ እግዚአብሄርን ማገልገል ሞኝነት ሲመስለው አይታችኋል?

መጠንቀቅ እንጂ እኔ እንደዚያ ልሆን አልችልም ማለት አያስፈልግም፡፡ ያም ሰው አንድ ቀን "እኔን አይመለከተኝም እኔ ልወድቅ አልችልም በጣም ሩቅ መጥቻለሁ" ሲል የነበረ ከመጠን ያለፈ መተማመን በራሱ የነበረው ሰው ነበር፡፡

እንደዚህ አይነት ሰው የወደቀበትን ውድቀት ስናይ ከዚህ በፊት ጌታን ተረድቶት እንደነበር እንጠራጠራለን፡፡ እውነቱ ግን ማንም ሰው ሊወድቅ ይችላል፡፡ ከዚህ ውድቀት አልፌያለሁ እኔን አይነካኝም ሊል የሚችል ሰው የለም፡፡

ስለዚህ ነው መፅሃፍ ቅዱስ "ፍራ እንጂ የትዕቢትን ነገር አታስብ" የሚለው፡፡ሮሜ 11:20

የልብ ችግር ከባድ ችግር ቢሆንም ነገር ግን መፍትሄ የሌለው ችግር አይደለም፡፡ ለዚህ የልብ ክፋት ችግር መፅሃፍ ቅዱስ ፍቱን መድሃኒት አለው፡፡
በመጀመሪያ ሰው እግዚአብሄርን የሚያስክደው ክፉና የማያምን ልብ እንዳይኖረው ሊጠነቀቅ ይገባዋል፡፡ የሚወድቀው የማይጠነቀቅና "እኔ ከመውደቅ አልፌያለሁ" የሚል ሰው ነው፡፡

መፅሃፍ ቅዱስ ልባችን በጥንቃቄ የምንከታተለው እንደሆነ ያስተምራል፡፡ ልባችንን በቸልታ ከያዝነው ሊያስተን የሚችል ትልቅ ሃይል ያለው ነው፡፡
ጌታን ብዙ ዓመት ከተከተልንና ካገለገልን በኋላ አንዳንዴ በልባችን የምናገኘው ክፉ ሃሳብ እኛን ራሳችንን ያስደነግጠናል፡፡እንደዚህ አይነት ሃሳብ ከእኔ ልብ ነው የወጣው ብለን አንድንጠይቅ ያስገድደናል፡፡

ከልብ ክፉ አሳብ፥ መግደል፥ ምንዝርነት፥ ዝሙት፥ መስረቅ፥ በውሸት መመስከር፥ ስድብ ይወጣልና። ማቴዎስ 15፡19

የሰው ልብ ከሁሉ ይልቅ ተንኰለኛ እጅግም ክፉ ነው፤ ማንስ ያውቀዋል? ኤርምያስ 17፡9

ልብን በጥንቃቄ መያዝ የሚበጀው ክፋት ሁሉ የሚወጣው ከልብ ስለሆነ ነው፡፡ ወንድሞች ሆይ፥ ምናልባት ሕያው እግዚአብሔርን የሚያስክዳችሁ ክፉና የማያምን ልብ ከእናንተ በአንዳችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፤ ዕብራውያን 3፡12

የሰውን ልብ የሚያውቅውና ሊገራው የሚችለው የእግዚአብሄርን ቃል ብቻ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ብቻ ነው ወደ ልባችን ሊደርስ የሚችለው፡፡ በልባችን ያለውን ነገር ሁሉ እንደ እንደእግዚአብሄር ፈቃድ የሚያሳየንና የሚያስተካክለው የእግዚአብሄር ቃል ብቻ ነው፡፡ በእግዚአብሄር ቃል ፊት ሁሉ ነገር የተገለጠና የተራቆተ ነው፡፡

የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤ እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ ዓይኖቹ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው እንጂ፥ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም። ዕብራውያን 4፡12-13

ስለዚህ ነው ከምንም ነገር በላይ የእግዚአብሄርን ቃል ለመስማት መትጋት ያለብን፡፡ ስለዚህ ነው ልባችንን በንፅህና ለመጠበቅ ማድረግ ያለብንን ነገር ሁሉ ማድረግ ያለብን፡፡ ስለዚህ ነው መፅሃፍ ቅዱስ "አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ፣ የሕይወት መውጫ ከእርሱ ነውና" የሚለው፡፡ ምሳሌ 4፡23

ስለዚህ ነው የእግዚአብሄር ቃልን ከሚያስቡና ከሚናገሩ ሰዎች ጋር በየእለቱ ህብረት ማድረግና መመካከር ክፉና የማያምን ልብ እንዳይኖረን መፍትሄ እንደሆነ የሚናገረው፡፡ ስለዚህ ነው ህይወታችን የእግዚአብሄርን ቃል በሚረዱ ሰዎች ፊት መፈተን ያለበት፡፡

የእግዚአብሄርን ቃል የሚረዱ እህቶችና ወንድሞች ናቸው እኛ ያላየነውን የልባችንን ክፋት የሚነግሩንና ልብህ ንፁህ አይደለም ብለው የሚገስፁን፡፡ 
ነገር ግን ከእናንተ ማንም በኃጢአት መታለል እልከኛ እንዳይሆን፥ ዛሬ ተብሎ ሲጠራ ሳለ፥ በእያንዳንዱ ቀን እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ፤ ዕብራውያን 3፡13

ይህንን ፅሁፍ ሼር ማድረግ ቢወዱ

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

#ተመካከሩ #ከሃዲ #እልከኛ #ልብ #ቃል #ምስጉን #ሃሳብ #ማሰላሰል #ወንጌል #ደቀመዝሙር #ኢየሱስ #ጌታ #መዳን #አማርኛ #ኢትዮጲያ #አቢይዋቁማ #ፌስቡክ #አዋጅ

Tuesday, September 20, 2016

አካባቢያችንን እንጠብቅ

ሰው አካባቢውን ከአየርና ከውሃ ብክለት ለመጠበቅ ታላቅ እንቅስቃሴ ይደረጋል፡፡ ሰዎች የአለምን አረንጓዴነትና ለጤና ተስማሚነት ለመጠበቅ ማንኛውም ነገር ያደርጋሉ፡፡
ምድርን የሚበክልን ነገር ለምሳሌ የከታላላቅ ፋብሪካዎች የሚወጣውን የተበከለ ጭስ እንዲቀነስ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ያደርጋሉ፡፡ ምክኒያቱም በቀጣይነት በቆሻሻ አካባቢ ውስጥ የሚኖር ሰው ከመታመምና ከመሞት ሊያመልጥ አይችልም፡፡
ከዚህ ሁሉ በላይ ግን አለማችንን የሚበክለው እግዚአብሄርን ባለማመንና ጥርጣሬ ነው፡፡ ሰው አካባቢውን በእግዚአብሄር ቃል ካልሞላ እግዚአብሄርን ካላመነ በስተቀር እግዚአብሄርን ደስ ሊያሰኝ ከእግዚአብሄር የሆነውንም ነገር ሊቀበል አይችልም፡፡ ከባቢው ተበላሽቶ እግዚአብሄርን ማመን ካቃተው ሰው የሚበልጥ ምስኪን ሰው የለም፡፡
ሰይጣን የሚመጣው ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ ነው፡፡ ሰይጣን የአስተሳሰብ አካባቢያችንን በመበከል መንፈሳዊ ጤንነታችንን የሚጎዱ ነገሮችን ሊያስፋፋ ይመጣል፡፡
የሰይጣን የመስረቂያ የማረጃና የማጥፊያ አካባቢዎች አለማመን ፍርሃትና ጥርጣሬ ናቸው፡፡
ስለዚህ ነው መፅሃፍ ቅዱስ አካባቢያችንን በእግዚአብሄር ቃል እንድንሞላና ንፅህናውን ከአለማመን እንድንጠብቅ የሚያስተምረን፡፡ አካባቢያችን በእግዚአብሄር ቃል ስንሞላና የእግዚአብሄርን ቃል ስንሰማ ንፁህ መንፈሳዊ አየርን መተንፈስ እንችላለን፡፡
የእስራኤል ህዝብ እግዚአብሔርን በፍጹም ልብ በፍጹምም ነፍስ በፍጹምም ኃይል ለመውደድ አካባቢያቸውን በእግዚአብሄር ቃል እንዲሞሉና ከብክለት እንዲጠብቁና እንዲያፀዱ ተመክረዋል፡፡
አንተም አምላክህን እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም ኃይልህ ውደድ። እኔም ዛሬ አንተን የማዝዘውን ይህን ቃል በልብህ ያዝ። ለልጆችህም አስተምረው፥ በቤትህም ስትቀመጥ፥ በመንገድም ስትሄድ፥ ስትተኛም፥ ስትነሣም ተጫወተው። በእጅህም ምልክት አድርገህ እሰረው፤ በዓይኖችህም መካከል እንደክታብ ይሁንልህ። በቤትህም መቃኖች በደጃፍህም በሮች ላይ ጻፈው። ዘዳግም 6፡5-9
የእግዚአብሄር ህዝብ መሪ የነበረው ኢያሱ የእግዚአብሄርን ቃል ለመፈፀም እንዲያስችለው ቃሉን በቀንና በሌሊት እንዲያሰላስልና በቃሉ አካባቢ ውስጥ እንዲኖር ታዟል፡፡
የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም። እያሱ 1፡8
እግዚአብሄር እንደልቤ ያለው መዝሙረኛው ዳዊት መዝሙሩን የጀመረው አካባቢውን ከክፋት ሃሳብ ብክለት ስለሚጠብቅና በእግዚአብሄር ቃል ከባቢ ውስጥ ስለሚኖረው ሰው ምስጉንነትና የዘወትር ክንውን በመናገር ነው፡፡
ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ። ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል። እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል። መዝሙር 1፡1-3
ሃዋሪያው ሰው አለምን የማይመስልበትን ብቸኛው መንገድ የሃሳብን አካባቢ በእግዚአብሄር ቃል በማፅዳትና በመጠበቅ እንደሆነ ያስተምራል፡፡
የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። ሮሜ 12፡2
መንፈሳዊ ህይወታችንን ከብክለት ለመጠበቅ በአስተሳሰብ አካባቢያችን የሚፈቀድላቸውና የማይፈቀድላቸው ነገሮች ሊኖሩ እንደሚገቡ መፅሃፍ ቅዱስ በአፅንኦት ያስተምራል፡፡
በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ እውነተኛ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ጭምትነት ያለበትን ነገር ሁሉ፥ ጽድቅ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ንጹሕ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ፍቅር ያለበትን ነገር ሁሉ፥ መልካም ወሬ ያለበትን ነገር ሁሉ፥ በጎነት ቢሆን ምስጋናም ቢሆን፥ እነዚህን አስቡ፤ ፊሊጲስዮስ 4፡8
ስለዚህ ነው ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱን ምን እንደምትሰሙ ተጠበቁ ያላቸው፡፡
አላቸውም፦ ምን እንድትሰሙ ተጠበቁ። ማርቆስ 4፡24
ስለዚህ ነው የእግዚአበሄር ቃል በቤታችን በስልኮቻችን በመኪናችን ልንሰማና ልናነብ የሚገባን፡፡ ለዚህ ነው ባገኘነው አጋጣሚ የእግዚአብሄርን ቃል ከባቢ መፍጠር ያለብን፡፡ ለዚህ ነው የእግዚአብሄርን ቃል ባገኘነው አጋጣሚ ሁሉ መጫወት ያለብን፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ለመስማት ለመረዳትና ለመጠበቅ የእግዚአብሄርን ቃል አካባቢ መፍጠርና በከባቢው ውስጥ መኖር አለብን፡፡ ስለዚህ ነው መፅሃፍ ቅዱስ አጥብቀህ አካባቢህን ጠብቅ ያለው፡፡
ልጄ ሆይ፥ ንግግሬን አድምጥ ወደ ቃሌም ጆሮህን አዘንብል። ከዓይንህ አታርቃት፥ በልብህም ውስጥ ጠብቃት። ለሚያገኙአት ሕይወት፥ ለሥጋቸውም ሁሉ ፈውስ ነውና። አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ፥ የሕይወት መውጫ ከእርሱ ነውና። ምሳሌ 4፡20 ፣ 22-23
አንተም አምላክህን እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም ኃይልህ ውደድ። እኔም ዛሬ አንተን የማዝዘውን ይህን ቃል በልብህ ያዝ። ለልጆችህም አስተምረው፥ በቤትህም ስትቀመጥ፥ በመንገድም ስትሄድ፥ ስትተኛም፥ ስትነሣም ተጫወተው። በእጅህም ምልክት አድርገህ እሰረው፤ በዓይኖችህም መካከል እንደክታብ ይሁንልህ። በቤትህም መቃኖች በደጃፍህም በሮች ላይ ጻፈው። ዘዳግም 6፡5-9
ይህንን ፅሁፍ ሼር ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes