Popular Posts

Wednesday, June 8, 2016

ወደ ፈተና አለመግባት ይቻላል

ብዙ ሰዎች ስለፈተና ያላቸው እውቀት ውስን ስለሆነ ፈተና በቀላሉ ይጥላቸዋል፡፡ ስለፈተና ምንም ማድረግ እንደማይችሉ እድላቸውን ብቻ እንደሚሞክሩ ይሰማቸዋል፡፡ ነገር ግን ስለፈተና የሆነ ነገር ማድረግ ይቻላል፡፡
ፈተና ፈተና ነው፡፡ ፈተናን ለማለፍ እውቀትን ጥንቃቄንና ትጋትን ይጠይቃል፡፡ ፈተና የሚመጣው ካልተዘጋጀን ሊጥለን ነው፡፡ ወደ ፈተና አለመግባት ማለት ፈተናው በእኛ ላይ ያለው እኛን የመጣል አላማ ሳይሳካለት ሲቀርና ፈተናውን በድል ስናልፈው ነው፡፡
ወደ ፈተና አለመግባት ግን እንዴት ደስ የሚል ነገር ነው ? ብዙ ሰዎች ግን ለፈተናው ያልበቁ ሆነው በፈተና ወድቀዋል፡፡ ከመንገዳቸውም ተሰናክለዋል፡፡
ወደፈተና አለመግባት ይቻላል፡፡
ተፈትኖ ማለፍን የመሰለ የሚያስደስት ነገር የለም፡፡ ደስ የሚለው ነገር ደግሞ ወደ ፈተና አለመግባት ይቻላል፡፡ ፈተና በሞላበት አለም ወደፈተና አለመግባት እንዴት ድንቅ እድል ነው፡፡
ችግሩ በምቹና በሰላሙ ጊዜ ፈተና የሚመጣ የሚመጣም አይመስል፡፡ ፈተና እጅግ ሩቅ ቦታ ያለና ለመምጣት ብዙ ጊዜ የሚፈጅበት ነው የሚመስለው፡፡ ባይመስልም ግን ፈተና መምጣቱ አይቀርም፡፡ ፈተና ግን ቢመጣ ሳይሆን ሲመጣ ነው የሚባለው፡፡ በዚያ ላይ መቼም እንደሚመጣ አለማወቃችንም ነው ፈተናን ፈተና ያደረገው፡፡ ፈተና አዘጋጅቶ አስጠንቅቅ 1 2 3 ብሎ ቆጥሮ አይመጣም፡፡ ፈተና ድንገት ነው የሚመጣው፡፡
መልካሙ የምስራች ግን ፈተና መጥቶ በእኛ ላይ ግን አንዳች እንዳያደርግና በሰላም እንድናልፈው ማድረግ እንደሚቻል መፅሃፍ ቅዱስ ያስተምራል፡፡ እየሱስ ፈተና ሲመጣ እንዳይጥለንና እንዳይወስደን ምን ማድረግ እንዳለብን ይናገራል፡፡
ፈተና ሳይመጣ በሰላሙ ቀን በምቾቱ ቀን ለፈተና ቀን በሚገባ መዘጋጀት ይቻላል፡፡ ወደፈተና አለመግባት የሚቻለው ተግቶ በመፀለይ ነው፡፡
ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ፀልዩ፣ ማቴዎስ 26፡41

ለተጨማሪ ፅሁፎች
https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

No comments:

Post a Comment