Popular Posts

Sunday, June 12, 2016

ፍርድ ሲዛባ


ብዙ ጊዜ ሳናውቀው ጥሩ የሰራን እየመሰለን የሚያስፈርድብንን ነገር ስናደርግ እንገኛለን፡፡ አትፍረዱ አይፈረድባችሁምም ይላል እየሱስ ሲያስተምር፡፡

አባታችሁ ርኅሩኅ እንደ ሆነ ርኅሩኆች ሁኑ። አትፍረዱ አይፈረድባችሁምም፤ አትኰንኑ አትኰነኑምም። ይቅር በሉ ይቅርም ትባላላችሁ። ሉቃስ 6፡36-37

·         የፍርድ ችግሩ ፈራጁ ራሱ ህጉን አይጠብቅም፡፡ የፈሪሳዊያን ችግር ለመፍረድና ለመቅጣት ፈጣን ናቸው፡፡ እነርሱ ግን በተመሳሳይ በደል ውስጥ የሚኖሩ ግብዞች ናቸው፡፡

ጻፎችና ፈሪሳውያን በሙሴ ወንበር ተቀምጠዋል። ስለዚህ ያዘዙአችሁን ሁሉ አድርጉ ጠብቁትም፥ ነገር ግን እየተናገሩ አያደርጉትምና እንደ ሥራቸው አታድርጉ። ከባድና አስቸጋሪ ሸክም ተብትበው በሰው ትከሻ ይጭናሉ፥ እነርሱ ግን በጣታቸው ስንኳ ሊነኩት አይወዱም። ማቴዎስ 23፡2-4

·         የመፍረድ ስህተቱ ሰው በሚሰፍርበት በዚያው መስፈሪያ ቢሰፈርለት ለእርሱ ይጎዳዋል እንጂ አይጠቅመውም፡፡

እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፥ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል። ማቴዎስ 7፡1-2

·         የመፍረድ ችግሩ የቤተሰብነት ስሜት ከማጣት የሚመነጭ ስለሆነ ነው፡፡ የሚፈርድ ሰው የራሱን ገመና ከመሸፈን ይልቅ የሚያማው የራሱን ቤተሰብ አባል ነው፡፡

ወንድሞች ሆይ፥ እርስ በርሳችሁ አትተማሙ። ወንድሙን የሚያማ በወንድሙም የሚፈርድ ሕግን ያማል በሕግም ይፈርዳል፤ በሕግም ብትፈርድ ፈራጅ ነህ እንጂ ሕግን አድራጊ አይደለህም። ሕግን የሚሰጥና የሚፈርድ አንድ ነው፤ እርሱም ሊያድን ሊያጠፋም የሚችል ነው፤ በሌላው ግን የምትፈርድ አንተ ማን ነህ? ያዕቆብ 4፡11-12

·         የሚፈርድ ሰው ሌሎች ህጉን እንዲጠብቁ እንደሚረዳ ምንም ማረጋገጫ የለውም፡፡ ሰዎች ህጉን እንዲፈፅሙ ምንም የሚያደርገው አስተዋፅኦ ስለሌለ የሚፈርድ ሰው ህጉን እንደሚያማ ይቆጠራል፡፡ የሚፈርድ ህጉ ሊፈፀም የማይችል ከባድ ነገር እንደሆነ ነው የሚያመለክተው እንጂ ሰው ህጉ እንዲፈፅም የሚያበረክተው ምንም አስተዋፅኦ የለም፡፡

 
በሕግም ብትፈርድ ፈራጅ ነህ እንጂ ሕግን አድራጊ አይደለህም። ወንድሙን የሚያማ በወንድሙም የሚፈርድ ሕግን ያማል በሕግም ይፈርዳል፤ ያዕቆብ 4፡11

·         የሚፈርድ ሰው እራሱ ደግሞ እንደሚፈረድበት ሰው ትሁት ያላደረገ ነገር ግን በፈራጅ ቦታ የተቀመጠና አብሮት የሚፈረድበት ሰው ላይ በክፉ ሃሳብ ሊፈርድ የሚሞክር ትምክተኛ ነው፡፡ በክፉ ሃሳብ የምንፈርድ ሰዎች አንሁን፡፡ ክፉ አሳብ ያላቸውም ዳኞች መሆናችሁ አይደለምን?ያዕቆብ 2፡4
 

ሕግን የሚሰጥና የሚፈርድ አንድ ነው፤ እርሱም ሊያድን ሊያጠፋም የሚችል ነው፤ በሌላው ግን የምትፈርድ አንተ ማን ነህ? ያዕቆብ 4፡12

አትፍረዱ አይፈረድባችሁምም፤

 

No comments:

Post a Comment