Popular Posts

Thursday, June 30, 2016

ታመን

በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፡፡ ምሳሌ 3፡5

ህይወት የእግዚአብሄር ውድ ስጦታ ነው፡፡ ይህን ስጦታ በሚገባ መያዝና መጠቀም ማስተዋል ይጠይቃል፡፡ የህይወትን ስጦታ በሚገባ ለመጠቀም ወደ ሰጭው መመለስና ለምን እንደሰጠንና ምን እንድናደርግበት እንደሰጠን መረዳት ይጠይቃል፡፡

በሌላ አነጋገር በምድር ላይ ለእግዚአብሄር ክብር ለመኖር ሁልጊዜ በእግዚአብሄር ምሪት ላይ መደገፍ ይጠበቅብናል፡፡


የእግዚአብሄርን ስጦታ ህይወትን በራስህ ማስተዋል አትኖረውም፡፡ የእግዚአብሄርን የህይወት ስጦታ በእግዚአብሄር እውቀትና ምሪት መጠቀም ይጠይቃል፡፡

ሁል ጊዜ በራሳችን እውቀትና ማስተዋል ነገሮችን ለማድረግ እንፈተናለን፡፡ ነገር ግን የራሳችን ማስተዋል ያስተናል እንጂ የትም አያደርሰንም፡፡

አሳቤ እንደ አሳባችሁ መንገዳችሁም እንደ መንገዴ አይደለምና ይላል እግዚአብሔር፦ ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፥ እንዲሁ መንገዴ ከመንገዳችሁ አሳቤም ከአሳባችሁ ከፍ ያለ ነው። ኢሳያስ 55፡8-9

በእግዚአብሄር የምትታመነውና የምትደገፈው ለእግዚአብሄር አዋቂነትና ፍፁም መሪነትና እውቅና በመስጠት ነው፡፡ ይህን በማለት ለእግዚአብሄር እውቅና ልንሰጥ ይገባናል፡፡

• እኔ ከመፈጠሬ በፊት ለእኔ ያቀድከው ሃሳብ አለ
• የእኔ የህይወት እቅድና ንድፍ በአንተ ዘንድ አለ
• እኔ ለራሴ ከማውቀው በላይ አንተ ለእኔ ታውቃለህ
• አንተ ለእኔ ያለህ አላማ የፍቅር አላማ ነው
• አንተ ለእኔ የምታስበው ሃሳብ መልካም ብቻ ነው

በማለት ይህንን እግዚአብሄር ለህይወታችን ያለውን ሃሳብ ከእግዚአብሄር መፈለግና መከተል መንገዳችን እንዲቃና ያደርጋል፡፡

ምሳሌ 3፡6 በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል።

ለተጨማሪ ፅሁፎች

Wednesday, June 29, 2016

በሃይማኖት ብትኖሩ



ብዙ ጊዜ እውነት በሃይማኖት ነኝ ብለን እንጠይቃለን፡፡ በህይወት ዘመን ሊመለስ የሚገባው ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡ ብዙ ጥያቄዎችን መመለስ እንኳን ባንችል ይህን በሃይማኖት ነኝን የሚለው ጥያቄ ከመለስን ይበቃል፡፡

በሃይማኖት መኖራችን ዘላለማችንን የት እንደምናሳልፍ ይወስነዋል፡፡ በሃይማኖት ብንኖር ለዘላለም ከእግዚአብሄር ጋር እንኖራልን፡፡ በሃይማኖት ካልኖርን ለዘላለም ከእግዚአብሄር ተለይተን ለሰይጣንንና ለመላእክቱ በተዘጋጀው እሳት ባህር ውስጥ እንጣላለን፡፡

ግን በሃይማኖት መሆናችን እንዴት ይታወቃል? በሃይማኖት ለመኖር ምንድ ነው ብቁ የሚያደርገን? እግዚአብሄርን ለማስደሰት ብቃትን የሚሰጠን ምንድነው ?

የማናችንም አስተያየት እዚህ ጋር አይሰራም፡፡ መፅሃፍ ቅዱስ ለዚህ መልስ አለው፡፡

በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ፤ ወይስ ምናልባት የማትበቁ ባትሆኑ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ እንዳለ ስለ እናንተ አታውቁምን? 2ኛ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡5

እየሱስ ስለሃጢያቴ ሞቷል በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነስቷል ብሎ የሚያምንና እየሱስ ጌታ እንደሆነ የሚመሰክር ሰው እግዚአብሄር ይቀበለዋል፡፡ እየሱስም በውስጡ መኖር ይጀምራል፡፡

ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና። ሮሜ 109-10

ብቁ የሚያደርገን የራሳችን መልካም ስራ ሳይሆን እየሱስ ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ የከፈለውን ዋጋ ለእኔ ነው እየሱስ የሞተው በእኔ ምትክ ነው ብለን እየሱስን ወደልባችን መቀበላችን ነው፡፡ ብቃታችን እየሱስ በልባችን በውስጣችን መኖሩ ነው፡፡
በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ፤ ወይስ ምናልባት የማትበቁ ባትሆኑ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ እንዳለ ስለ እናንተ አታውቁምን? 2ኛ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡5

ለተጨማሪ ፅሁፎች 




የራስ ጥፋት

ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት።
ይገርማል ፡፡ ሰይጣን በህይወታችን መግቢያ ካገኘ ስፍራ የሰጠነው እኛ ነን ማለት ነው፡፡ ምክኒያቱም እየሱስ በመስቀል ላይ ሲሰቀል የሰይጣንን ሃይልና ስልጣን ሁሉ ገፎታል፡፡
አለቅነትንና ሥልጣናትን ገፎ፥ ድል በመንሣት በእርሱ እያዞራቸው በግልጥ አሳያቸው። ቆላስይስ 2፡15
እርሱ ከጨለማ ሥልጣን አዳነን፥ ቤዛነቱንም እርሱንም የኃጢአትን ስርየት ወዳገኘንበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሥት አፈለሰን። ቆላስይስ 2፡13-14
ሰይጣን በህይወታችን ስፍራ የሚያገኘው እኛው ከሰጠነው ብቻ ነው፡፡ ከዚያ ውጭ በግድ ምንም ስፍራ ሊወስድ አይችልም፡፡
ሰይጣን በምድር ላይ ለእግዚአብሄር እየኖርን የእግዚአብሄርን ስራ እንድንሰራ በፍፁም አይፈልግም፡፡ ቢችል ከምድረ ገፅ ያጠፋናል፡፡ እኛ የምንኖረው በሰይጣን ምህረት አይደለም ፡፡ ሰይጣን ስለፈቀደልንና አስኮናኞች ኑሩ ብሎ ስለተወን አይደለም የምንኖረው ፡፡
ለእግዚአብሄር የምንኖረውና እግዚአብሄርን የምናገለግለው በሃይልና በስልጣን ነው፡፡ 
ግን ደግሞ ከፈቀድንለት እንደፈቀድንለት መጠን ሊሰርቅ ሊያርድና ሊያጠፋ ወደህይወታችን ይመጣል፡፡ ዮሃንስ 10፡10 
ግን ለሰይጣን ስፍራ መስጠት ማለት ምን ማለት ነው? 
ለሰይጣን ስፍራን መስጠት ልብን በንፅህና አለመጠበቅ ነው፡፡ 
ሰው በቁጣው ላይ ፀሃይ ሲገባና ምሬት ውስጥ ሲገባ ያ በህይወቱ ለሰይጣን በርን ይከፍታል፡፡ ሰይጣን በሰዎች ህይወት የሚሰራው ጥላቻን በህይወታቸው ሲያገኝ ብቻ ነው፡፡ 
ሰይጣን በሰዎች ህይወት የሚሰራው ሰዎች ፍቅርን ጥለው በራስ ወዳድነት ሲኖሩ ብቻ ነው፡፡ 
ቆሻሻ ዝንብን እንደሚጠራ ሁሉ ጥላቻና ራስ ወዳድነት ሰይጣንን ይጠራል፡፡ ጥላቻና ፍቅር ማጣት ለሰይጣን መራቢያ ለም መሬቱ ነው፡፡ ምሬትንና ጥላቻን ከህይወታችን ካስወገድን በህይወታችን ለሰይጣን ስፍራን እንከለክለዋለ፡፡ 
ተቆጡ ኃጢአትንም አታድርጉ፤ በቁጣችሁ ላይ ፀሐይ አይግባ፥ ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት። ኤፌሶን 4፡26-27

Tuesday, June 28, 2016

በሃይማኖት ብትኖሩ

ብዙ ጊዜ እውነት በሃይማኖት ነኝ ብለን እንጠይቃለን፡፡ በህይወት ዘመን ሊመለስ የሚገባው ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡ ብዙ ጥያቄዎችን መመለስ እንኳን ባንችል ይህን በሃይማኖት ነኝን የሚለው ጥያቄ ከመለስን ይበቃል፡፡
በሃይማኖት መኖራችን ዘላለማችንን የት እንደምናሳልፍ ይወስነዋል፡፡ በሃይማኖት ብንኖር ለዘላለም ከእግዚአበሄር ጋር እንኖራልን፡፡ በሃይማኖት ካልኖርን ለዘላለም ከእግዚአብሄር ተለይተን ለሰይጣንንና ለመላእክቱ በተዘጋጀው እሳት ባህር ውስጥ እንጣላለን፡፡

ግን በሃይማኖት መሆናችን እንዴት ይታወቃል? በሃይማኖት ለመኖር ምንድ ነው ብቁ የሚያደርገን? እግዚአብሄርን ለማስደሰት ብቃትን የሚሰጠን ምንድነው ?

የማናችንም አስተያየት እዚህ ጋር አይሰራም፡፡ መፅሃፍ ቅዱስ ለዚህ መልስ አለው፡፡

በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ፤ ወይስ ምናልባት የማትበቁ ባትሆኑ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ እንዳለ ስለ እናንተ አታውቁምን? 2ኛ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡5

እየሱስ ስለሃጢያቴ ሞቷል በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነስቷል ብሎ የሚያምንና እየሱስ ጌታ እንደሆነ የሚመሰክር ሰው እግዚአብሄር ይቀበለዋል፡፡ እየሱስም በውስጡ መኖር ይጀምራል፡፡

ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና። ሮሜ 10፡9-10

ብቁ የሚያደርገን የራሳችን መልካም ስራ ሳይሆን እየሱስ ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ የከፈለውን ዋጋ ለእኔ ነው እየሱስ የሞተው በእኔ ምትክ ነው ብለን እየሱስን ወደልባችን መቀበላችን ነው፡፡ ብቃታችን እየሱስ በልባችን በውስጣችን መኖሩ ነው፡፡

በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ፤ ወይስ ምናልባት የማትበቁ ባትሆኑ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ እንዳለ ስለ እናንተ አታውቁምን? 2ኛ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡5

በሃይማኖት ብትኖሩ

ብዙ ጊዜ እውነት በሃይማኖት ነኝ ብለን እንጠይቃለን፡፡ በህይወት ዘመን ሊመለስ የሚገባው ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡ ብዙ ጥያቄዎችን መመለስ እንኳን ባንችል ይህን በሃይማኖት ነኝን የሚለው ጥያቄ ከመለስን ይበቃል፡፡
በሃይማኖት መኖራችን ዘላለማችንን የት እንደምናሳልፍ ይወስነዋል፡፡ በሃይማኖት ብንኖር ለዘላለም ከእግዚአበሄር ጋር እንኖራልን፡፡ በሃይማኖት ካልኖርን ለዘላለም ከእግዚአብሄር ተለይተን ለሰይጣንንና ለመላእክቱ በተዘጋጀው እሳት ባህር ውስጥ እንጣላለን፡፡

ግን በሃይማኖት መሆናችን እንዴት ይታወቃል? በሃይማኖት ለመኖር ምንድ ነው ብቁ የሚያደርገን? እግዚአብሄርን ለማስደሰት ብቃትን የሚሰጠን ምንድነው ?

የማናችንም አስተያየት እዚህ ጋር አይሰራም፡፡ መፅሃፍ ቅዱስ ለዚህ መልስ አለው፡፡

በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ፤ ወይስ ምናልባት የማትበቁ ባትሆኑ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ እንዳለ ስለ እናንተ አታውቁምን? 2ኛ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡5

እየሱስ ስለሃጢያቴ ሞቷል በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነስቷል ብሎ የሚያምንና እየሱስ ጌታ እንደሆነ የሚመሰክር ሰው እግዚአብሄር ይቀበለዋል፡፡ እየሱስም በውስጡ መኖር ይጀምራል፡፡

ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና። ሮሜ 10፡9-10

ብቁ የሚያደርገን የራሳችን መልካም ስራ ሳይሆን እየሱስ ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ የከፈለውን ዋጋ ለእኔ ነው እየሱስ የሞተው በእኔ ምትክ ነው ብለን እየሱስን ወደልባችን መቀበላችን ነው፡፡ ብቃታችን እየሱስ በልባችን በውስጣችን መኖሩ ነው፡፡

በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ፤ ወይስ ምናልባት የማትበቁ ባትሆኑ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ እንዳለ ስለ እናንተ አታውቁምን? 2ኛ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡5

ፈጣን ባለጠግነት

የታመነ ሰው እጅግ ይባረካል ባለጠጋ ለመሆን የሚቸኵል ግን ሳይቀጣ አይቀርም። ምሳሌ 28፡20
እግዚአብሄር በልጆቹ ብልፅግና መሳካትና መከናወን ደስ ይለዋል፡፡ እግዚአብሄር ይባርካል፡፡ እግዚአብሄር በማንም መባረክና ማግኘት ላይ ተቃውሞ የለውም፡፡ እንዲያውም መፅሃፍ ደስም እንዲለን ሁሉን አትርፎ በሚሰጠን በሕያው እግዚአብሔር እንድንመካ ያስተምረናል፡፡ 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡17 
የሰው ታማኝነት የሚታየው በአንድ ቀንና በአንድ ወር አይደለም፡፡ የሰው ታማኝነት የሚታየው በጊዜያት ውስጥ ነው፡፡ የታመነ ሰው በመታመን በቀጠለ መጠን ጥቂት በጥቂት እየጨመረ እየተባረከና እየበዛ ይሄዳል፡፡ 
እግዚአብሄር የራሱ እርምጃና ፍጥነት አለው፡፡ነገር ግን እግዚአብሄር በአንዴ አያሳድግም፡፡ 
ባለጠጋ ለመሆን መቸኮል ግን ችግር ነው፡፡ ፈጣኑ ባለጠግነት የእግዚአብሄር እጅ የለበትም፡፡ ፈጣኑ ባለጠግነት በፍፁም በንፅህና የሚመጣ አይደለም፡፡ ፈጣኑ ባለጠግነትና ከእግዚአብሄር ውጭ የሚመጣ ነው፡፡ 
ባለጠጋ ለመሆን የሚቸኩል ወይ ያጭበረብራል ወይ ይሰርቃል ወይ ይገድላል፡፡ ባለጠጋም ለመሆን ቸኩሎም ንፁህም መሆን አይቻልም፡፡ ባለጠጋ ለመሆን ቸኩሎም የእግዚአብሄርን በረከትንም ጠብቆም አይሆንም፡፡ 
ሰው ባለጠጋ ለመሆን ከቸኮለ የእግዚአብሄርን እርምጃ አልታገሰም ፡ እግዚአብሄርን በትግስት አልጠበቀም እንዲሁም የእግዚአብሄርን የበረከት መንገድ ትቶታል ማለት ነው፡፡ 
እግዚአብሄር የሚሰጠው ሃብት መሰረት ያለው ነው ሃዘንንም ከእርሱ ጋር አይጨምርም፡፡ 
የእግዚአብሔር በረከት ባለጠጋ ታደርጋለች፥ ኀዘንንም ከእርስዋ ጋር አይጨምርም። ምሳሌ 10፡22
በችኮላ የምትከማች ሃብት ግን የእግዚአብሄር እጅና ድጋፍ ስለሌለባት መሰረት እንደሌላት ቤት ነች፡፡ ተግንብታ ስታልቅ ከስርዋ ትናዳለች፡፡ 
በችኰላ የምትከማች ሀብት ትጐድላለች ጥቂት በጥቂት የተከማቸች ግን ትበዛለች። ምሳሌ 13፡11

ፈጣን ባለጠግነት

የታመነ ሰው እጅግ ይባረካል ባለጠጋ ለመሆን የሚቸኵል ግን ሳይቀጣ አይቀርም። ምሳሌ 28፡20
እግዚአብሄር በልጆቹ ብልፅግና መሳካትና መከናወን ደስ ይለዋል፡፡ እግዚአብሄር ይባርካል፡፡ እግዚአብሄር በማንም መባረክና ማግኘት ላይ ተቃውሞ የለውም፡፡ እንዲያውም መፅሃፍ ደስም እንዲለን ሁሉን አትርፎ በሚሰጠን በሕያው እግዚአብሔር እንድንመካ ያስተምረናል፡፡ 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡17 
የሰው ታማኝነት የሚታየው በአንድ ቀንና በአንድ ወር አይደለም፡፡ የሰው ታማኝነት የሚታየው በጊዜያት ውስጥ ነው፡፡ የታመነ ሰው በመታመን በቀጠለ መጠን ጥቂት በጥቂት እየጨመረ እየተባረከና እየበዛ ይሄዳል፡፡ 
እግዚአብሄር የራሱ እርምጃና ፍጥነት አለው፡፡ነገር ግን እግዚአብሄር በአንዴ አያሳድግም፡፡ 
ባለጠጋ ለመሆን መቸኮል ግን ችግር ነው፡፡ ፈጣኑ ባለጠግነት የእግዚአብሄር እጅ የለበትም፡፡ ፈጣኑ ባለጠግነት በፍፁም በንፅህና የሚመጣ አይደለም፡፡ ፈጣኑ ባለጠግነትና ከእግዚአብሄር ውጭ የሚመጣ ነው፡፡ 
ባለጠጋ ለመሆን የሚቸኩል ወይ ያጭበረብራል ወይ ይሰርቃል ወይ ይገድላል፡፡ ባለጠጋም ለመሆን ቸኩሎም ንፁህም መሆን አይቻልም፡፡ ባለጠጋ ለመሆን ቸኩሎም የእግዚአብሄርን በረከትንም ጠብቆም አይሆንም፡፡ 
ሰው ባለጠጋ ለመሆን ከቸኮለ የእግዚአብሄርን እርምጃ አልታገሰም ፡ እግዚአብሄርን በትግስት አልጠበቀም እንዲሁም የእግዚአብሄርን የበረከት መንገድ ትቶታል ማለት ነው፡፡ 
እግዚአብሄር የሚሰጠው ሃብት መሰረት ያለው ነው ሃዘንንም ከእርሱ ጋር አይጨምርም፡፡ 
የእግዚአብሔር በረከት ባለጠጋ ታደርጋለች፥ ኀዘንንም ከእርስዋ ጋር አይጨምርም። ምሳሌ 10፡22
በችኮላ የምትከማች ሃብት ግን የእግዚአብሄር እጅና ድጋፍ ስለሌለባት መሰረት እንደሌላት ቤት ነች፡፡ ተግንብታ ስታልቅ ከስርዋ ትናዳለች፡፡ 
በችኰላ የምትከማች ሀብት ትጐድላለች ጥቂት በጥቂት የተከማቸች ግን ትበዛለች። ምሳሌ 13፡11

Monday, June 27, 2016

የሚያስፈልጋችሁን

እንግዲህ። ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ማቴዎስ 6፡31-32
 
እግዚአብሄር የሚያዘጋጀው የሚያስፈልገንን ነው፡፡ በሚያስገልገን መጠን ነው እግዚአብሄር የሚያቀርበው፡፡ 
 
እግዚአብሄር ተረፍ አድርጎ ካቀረበና አሁን ከሚያስፈልገን በላይ ከሰጠን እንኳን ያ ማለት ሌላ የሚያስፈልገን ነገር እየመጣ ነው ማለት ነው፡፡ 
 
ተረፍ ብሎ ካልመጣ ደግሞ እግዚአብሄር ይመስገን ፍላጎት የለብንም ማለት ነው፡፡
 
እግዚአብሄር የሚያቀርበው እንደፍላጎታችን መጠን እንጂ እንደ ጎረቤታችንም አይደለም፡፡ የእኛና የጎረቤታችን ፍላጎት ይለያያል፡፡ እግዚአብሄር ለእኛና ለጎረቤታችን እኩል አያቀርብም፡፡ 
 
የእኛ አቅርቦት ከጎረቤታችን ከበለጠ ያ ማለት ይበልጥ ፍላጎት እየመጣብን ነው ማለት ነው፡፡ የጎረቤታችን ከእኛ ከበለጠ ደግሞ ጎረቤታችን የሚያስፈልገው ሁኔታ ላይ ነው ማለት ነው፡፡ 
 
ፅድቁንና መንግስቱን ስንፈልግ ምን እንደሚያስፈልገን የሚያውቅና የሚሰጥ አባት ማግኘትን የመሰለ ነገር የለም፡፡ 
 

Saturday, June 25, 2016

የማይታይ እጅ

ስለ እግዚአብሄር አሰራር የማይረዳ ሰው ይህን እድሌ ነው ይላል፡፡ እኛ ግን እግዚአብሄር ነው እንላለን፡፡
በሰው ልብ ብዙ አሳብ አለ፤ የእግዚአብሔር ምክር ግን እርሱ ይጸናል። ምሳሌ 19፡21
እግዚአብሄር እኛን ሁላችንን ፈጥሮናል፡፡ እግዚአብሄር ለህይወታችን የሚፈልገው ነገር አለ፡፡ እኛ ለህይወታችን የማንፈልገው ነገር እንዳለ ሁሉ ደግሞ እግዚአብሄርም ለህይወታችን የማይፈልገው ነገር አለ፡፡ ይህንን ምክሩን ለማስፈፀም እግዚአብሄር ምድርንና ሰማይን በሚገባ እየተቆጣጠረ እየመራ ነው ፡፡
ሰው በራሱ በልቡ ያለውን ነገር ሁሉ ቢያደርግ አለም ምን ልትሆን እንደምትችል መገመትም ያስቸግራል፡፡
በሰው ልብ ብዙ ሃሳብ ቢኖርም መጨረሻ ላይ የሚያይለውና የሚበረታውና የሚፈፀመውም የእግዚአብሄር ሃሳብ ነው፡፡
ይህን ማወቅ እንዴት ያሳርፋል፡፡ ምንም እንኳን በሰው ልብ ውስጥ ያለው ሃሳብ ብዙ ቢሆንም ግን በርትታ የምትወጣውና የምትፈፀመው የመልካሙ የአባታችን የእግዚአብሄር ሃሳብ መሆኑን ማወቅ እጅግ ደስ ያሰኛል፡፡
ይህንኑ ሃሳብ በብሉይ ኪዳን ቋንቋ እንዲህ በማለት ሰባኪው ይገልፀዋል ፡፡
እኔም ተመለስሁ፥ ከፀሐይ በታችም ሩጫ ለፈጣኖች፥ ሰልፍም ለኃያላን፥ እንጀራም ለጠቢባን፥ ባለጠግነትም ለአስተዋዮች፥ ሞገስም ለአዋቂዎች እንዳልሆነ አየሁ፤ ጊዜና እድል ግን ሁሉን ይገናኛቸዋል። መክብብ 9፡11
ይገርማል እግዚአብሄር አይሆንም ካለ የሩጫ ድል ለፈጣን አይሆንም፡፡
እግዚአብሄር ካልሰጠ ባለጠግነት በቅልጥፍና አይመጣም፡፡
እግዚአብሄር ይሁን ካላለ ሰው አዋቂነቱ ብቻ ሞገስን አይሰጠውም፡፡
ሁሉን የሚሰካካው የሚያገናኘው የጊዜና የእድል ባለቤቱ እግዚአብሄር ራሱ ነው፡፡
በሰው ልብ ብዙ አሳብ አለ፤ የእግዚአብሔር ምክር ግን እርሱ ይጸናል። ምሳሌ 19፡21

Friday, June 24, 2016

ህይወት ትርጉም

የከንቱ ከንቱ ሁሉ ከንቱ ነው ይላል ሰባኪው

በኢየሩሳሌም የነገሠ የሰባኪው የዳዊት ልጅ ቃል። ሰባኪው። ከንቱ፥ ከንቱ፥ የከንቱ ከንቱ ሁሉ ከንቱ ነው ይላል። ከፀሐይ በታች መክብብ 1፡1-3

አይገርምም ሰባኪው ሁሉ ከንቱ ነው ንፋስን እንደመከተል ነው ይላል፡፡ እውነት ነው ከፀሃይ በታች ሁሉ ከንቱ ነው የከንቱ ከንቱ፡፡

ሰባኪው ከፀሃይ በታች ምን ምን ከንቱ እንደሆነና ምንም ዋጋ እንደሌለው የሚናገረው ስለምን እንደሆነ እንመልከት፡፡

ከእግዚአብሄር የተለየ የሰው ጥበብ ከንቱ ነው፡፡ መክብብ 2፡14-16

በእግዚአብሄር ያልሆነ መስራት መልፋትና መድከም ከንቱ ነው፡፡ መክብብ 2፡14-16

እግዚአብሄር የሌለበት ነገሮችን ማከማቸት ንፋስን እንደመከተል ነው መክብብ 2፡26

ካለአላማ መኖር ከእግዚአብሄር ጋር ያልተዛመደና ያልተገናኘ ህይወት ራሱ ከንቱ ነው፡፡ መክብብ 3:18–22

በአለም ያለ እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ ውድድርና ቅንአት ከንቱ ነው፡፡ መክብብ 4:4

በስግብግብነት ያለቅጥ መስራት ከንቱ ነው፡፡ መክብብ 4:7-8

ሃይልና ለስልጣን ማከማቸት ከንቱነት ነው፡፡ መክብብ 4:16

ስስት ፡ ምኞትና አለመርካት ከንቱ ነው፡፡ መክብብ 5:10

የማይጠቀሙበት ሃብትና ቅንጦት ማከማቸት ንፋስን እንደመከተል ነው፡፡ መክብብ 6:1-2

ሰው በሰማይ አምላክ በእግዚአብሄር ተፈጥሮአል፡፡ ሰው ከእግዚብሄር ጋር ህብረት ማድረግ እንዲችል በመልኩና በአምሳሉ ተፈጥሮአል፡፡ሰው ለፈጣሪው ለእግዚአብሄር እውቅና በመስጠትና እርሱን በመፍራት በምድር ላይ ያዘጋጀለትን መልካም ስራ እንዲያደርግ ተፈጥሮአል፡፡
ሰው ከተፈጠረለት አላማ ውጭ ሲኖር ሁሉ ከንቱ ነው፡፡

ከዚህ ውጭ የሆነ ነገር ሁሉ ከንቱ የከንቱ ከንቱ ነው፡፡ ከእግዚአብሄር ጋር ግንኙነት ሲኖረን ነው እንጂ ፣ ከእግዚአብሄር ጋር ስንሰራ ነው እንጂ ፣ ለእግዚአብሄር ስንኖር ነው እንጂ እግዚአብሄርን ስናገለግል ነው እንጂ ከዚያ ውጭ ከፀሃይ በታች ያለ ነገር ሁሉ ከንቱ የከንቱ ከንቱ ነው፡፡ከእግዚአብሄር ውጭ ህይወት ትርጉም የለውም፡፡

ከእግዚአብሄር ውጭ ህይወት ዋጋ የለውም፡፡ሰው ለህይወቱ ትርጉም የሚያገኘው ለፈጠረው ለእግዚአብሄር እውቅና ሲሰጥና ለእርሱ ለመኖር ሲወስን ብቻ ነው፡፡

Thursday, June 23, 2016

የሚበልጥ ምርጫ

ዛሬ ለእንግሊዞች የምርጫ ቀን ነው፡፡ ምርጫ ደግሞ እድልን ይወስናል፡፡
 
እንግሊዝ ከአውሮፓ ህብረት ጋር ለመቆየትና ከአውሮፓ ህብረት ለመውጣት ህዝቡ ምርጫን ያደርጋል፡፡ ከህብረቱ መውጣት የሚያስከትለውን ጉዳትና በህብረቱ መቆየት ያለውን ጥቅም በማስረዳት የህብረቱ ደጋፊዎች አብዛኛው ሰው ህብረቱን እንዲመርጡ ይቀሰቅሳሉ፡፡
 
እንግሊዝ ከህብረቱ መውጣት ይሻላታል የሚሉ ወገኖችም እንዲሁ ከህብረቱ መለየት የሚጠቅመውን ጥቅምና በህብረቱ መቆየት የሚጎዳውን ጉዳት በመዘርዘር ከህብረቱ መውጣትን ብዙዎች እንዲመርጡ ሲቀሰቅሱ ቆይተዋል፡፡
 
ከህብረቱ መውጣትምን ሆነ በህብረቱ መቆየት ጥቅምም ጉዳትም ይኖረዋል፡፡ ይህ የምርጫ ጉዳይ ነው፡፡
 
ከእነዚህ ሁሉ እጅግ የበለጠ ጥቅም ያለውና ካልመረጥነው እጅግ የከፋ ጉዳት ያለው በህይወት ዘመናችን መምረጥ ያለብን ወሳኝ ምርጫ ደግሞ አለ፡፡ ይህ ምርጫ የምድር ኢኮኖሚያችንን ጤናችንንና ደህንነታችንን ብቻ ሳይሆን የዘላለም እጣ ፈንታችንን ነው የሚወስነው ፡፡
 
እግዚአብሄር እየሱስን ወደ ምድር ሲልከው ለሃጢያታችን እንዲሞትና በመስቀል ላይ የሃጢያታችንን እዳ እንዲከፍል ነው፡፡
 
ይህንን እየሱስ በመስቀል ላይ የከፈለውን የሃጢያት ዋጋ ለእኔ ነው ብሎ የሚቀበልና እየሱስን የሚመርጥ የዘላለም ህይወት ያገኛል፡፡ አይ የሚልና የእግዚአብሄርን ያዘጋጀውን የመዳኛ መንገድ የማይቀበል ለዘለአለም ከእግዚአብሄር በመለየት የዘላለም ፍርድ ያገኛል ፡፡
 
በምድር ላይ እየሱስን የሚመርጡና የእግዚአብሄር ልጅነትን ስልጣን የሚቀበሉ አሉ፡፡ በምድር ላይ እስከመጨረሻው እየሱስን የማይመርጡ አሉ፡፡
 
ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ ዮሃንስ 1፡12
 
በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። ዮሃንስ 3፡16
 
በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም። ዮሃንስ 3፡36


የስኬት ጣራ

ሁላችንም በክርስትና ህይወታችን ማደግና የመጨረሻው ደረጃ ላይ መድረስ እንፈልጋለን፡፡ 

የክርስትና ህይወት የእድገት ጫፍ ጣራው ምንድነው ? የሚለውን ጥያቄ መልስ ማወቃችን ደረጃው ላይ ስንደርስበት ያሳርፈናል በክርስትና የሚያስቀና ሰው ሚሊየነር የሆነ ሰው አይደለም፡፡

በክርስትና የሚያስቀና የመጨረሻው ሰው በሚሊየኖች ሰዎች ታዋቂ የሆነ ዝነኛ ሰው አይደለም፡፡ 

በክርስትና እርሱን ባደረገኝ ተብሎ የሚቀናበት ሰው ከሰው ሁሉ በላይ ሃያል የሆነ ሰው አይደለምን፡፡

በክርስትና ፐ የሚባልለትና የሚያስቀና ሰው የመጨረሻው ስኬታማና የተከናወነለት ሰው መሰረታዊ ፍላጎቱን አሟልቶ እግዚአብሄርን በመምሰል ጌታን የሚከተልና የሚያገለግል ሰው ነው፡፡

በክርስትና ከዚህ ደረጃ በላይ ደረጃ የለም፡፡ ይህ ለእግዚአብሄርም ለእኛም በቂ ነው፡፡

ኑሮዬ ይበቃኛል ለሚለው ግን እግዚአብሔርን መምሰል እጅግ ማትረፊያ ነው፤ . . . ምግብና ልብስ ከኖረን ግን፥ እርሱ ይበቃናል። 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡6 ፣ 8
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

Tuesday, June 21, 2016

ጥበብ ሀ ሁ

የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ሰነፎች ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ። ምሳሌ 1፡7
እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው ለራሱ ክብር ነው ፡፡ ሰው ለእግዚአብሄር ፈጣሪነትና ባለቤትነት እውቅና መስጠቱ በጣም አስፈላጊ ነው ፡፡ ይህን ብቻ ሳይሆን ሰው ከእግዚአብሄር ጋር እንዴት መኖር እንዳለበት ማወቅ ለሰው ልጅ ህይወት እውነተኛ ስኬት መሰረት ነው፡፡
ሰው ከፈጠረው ከእግዚአብሄር ጋር ያለው ግንኙነት ከተስተካከለ ከሌላ ከምንም ነገር ጋር ያለው ግንኙነት ሊስተካከል ይችላል፡፡ ነገር ግን ሰው ከፈጣሪው ጋር ያለው ግንኙነት ከተበላሸ ሌላ ምንም ነገር ሊሰምርለት አይችልም፡፡
ሰው በምድር ላይ በስጋ ለመኖርና በመንፈሳዊው አለም በነፍሱ በሚገባ ለመኖር እውቀትና ጥበብ በጣም አስፈላጊ ነገሮች ናቸው፡፡ ብዙ የእውቀትና የጥበብ አይነቶች ያሉ ሲሆን ለእያንዳንዱ የጥበብ አይነት መሰረቱ ሰው ከፈጣሪው ጋር የሚኖረው ግንኙነት እውቀት ነው፡፡
ሰው ከምንም ነገር ጋር ያለውን ግንኙነትን እንዴት ማስኬድ እንዳለበት ቢያውቅ ነገር ግን ከእግዚአብሄር ጋር ስላለው ግንኙነት ጥበብ የጎደለው አላዋቂ ቢሆን ጥበቡ መሰረት እንደሌለው ቤት ለምንም ነገር ዋጋ የሌለው ይሆናል፡፡
ስለዚህም እግዚአብሔርን እያወቁ እንደ እግዚአብሔርነቱ መጠን ስላላከበሩትና ስላላመሰገኑት የሚያመካኙት አጡ፤ ነገር ግን በአሳባቸው ከንቱ ሆኑ የማያስተውለውም ልባቸው ጨለመ። ጥበበኞች ነን ሲሉ ደንቆሮ ሆኑ፥ ሮሜ 1፡21-22
ለእግዚአብሄር የሚገባውን ስፍራ መስጠትና ለእግዚአብሄር አምላክነት እውቅና መስጠት የጥበብ መሰረት ነው፡፡ የጥበብ ሀሁ እግዚአብሄርን መፍራት ነው፡፡ ካለ ጥበብ ሀሁ የጥበብ አቡጊዳም ሆነ የጥበብ መልክተ ሊኖር አይችልም፡፡
በምድር ላይ በስኬት ለመኖር ዝቅተኛው መመዘኛ እግዚአብሄርን መፍራት ነው፡፡ እግዚአብሄርን መፍራት ከሞላ ጎደል ሁሉም መመዘኛ ነው፡፡ ይህ ዝቅተኛው መመዘኛ የጎደለው ሰው ምንም መመዘኛ እንዳላሟላ ይቆጠራል፡፡ ይህ ዝቅተኛውን መመዘኛ ያሟላ ሰው ግን ሌሎች ሰዎች የሚመኩባቸው ጥበቦች ቢጎሉትም ህይወቱ ይሰምራል፡፡ ይህ ከእግዚአብሄር ጋር ያለው ግንኙነት ጥበብ ጎድሎት የሚሳካለት ሰው ግን የለም፡፡
የነገሩን ሁሉ ፍጻሜ እንስማ፤ ይህ የሰው ሁለንተናው ነውና፤ እግዚአብሔርን ፍራ፥ ትእዛዙንም ጠብቅ። እግዚአብሔር ሥራን ሁሉ የተሰወረውንም ነገር ሁሉ፥ መልካምም ቢሆን ክፉም ቢሆን፥ ወደ ፍርድ ያመጣዋልና። መክብብ 12፡13-14
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ምሳሌ 1፡7

Sunday, June 19, 2016

አባት ሁን

እግዚአብሄር ሰውን ሲፈጥር ሰው እንዲበዛ እንዲባዛም አዟል፡፡ እግዚአብሄር ሰውን እንዲበዛ ያዘዘው በቤተሰብ ውስጥ ነው፡፡
እግዚአብሄር ያቀደው ልጅ በአባትና በእናት የማያቋርጥ የፍቅር እንክብካቤ ተሞልቶና ተኮትኩቶ እንዲያድግ ነው፡፡ ስለዚህ ነው ልጅ ያሳደጉት የአባቱና የእናቱ የፍቅር ግብአት ውጤት ነው የሚባለው፡፡
ልጅ በአባትና በእናት መካከል ባለ የመጨረሻው የፍቅር ግንኙነት እንዲወለድና በእናትና በአባት አማካኝነትና በእነርሱ መካከል እንዲያድግ እግዚአብሄር ያቀደው ለልጁ በቅርበት እንክብካቤ እንዲያደርጉለትና የቅርብ የህይወት ምሳሌ እንዲሆኑለት በማቀድ ነው፡፡
አንዳንድ ሰው ግን በቸልተኝነትና በራስ ወዳድነት ይህንን የአባትነት ሃላፊነት ቸል ሲልና ይህን አላማ ሲጥስ በዚህ ምክኒያት በምድር ላይ ብዙ ችግሮች ሲፈጠሩ ይታያል፡፡
በተለይ በምድር ላይ ያሉ የተለያዩ የአለማችንን ችግሮች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚፈጠሩት ወይም የሚባባሱት በልጅነታቸው እግዚአብሄር በቤተሰብ ውስጥ ያቀደላቸውን የሚገባቸውን የአባትነት ፍቅርና ርህራሄ ተነፍገው ባደጉ ሰዎች ነው፡፡
በአባት ስርአትና ዲሲፒሊን ተኮትኩቶ ያላደገ ልጅ ሃላፊነትን ሊወስድ የሚችል ሙሉ ሰው መሆን ይቸግረዋል፡፡ ስለዚህ ነው በአለም ላይ ያሉ ችግሮች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪም መንስኤው የአባት በልጅ ላይ ያለ ኢንቨስትመንት ጉድለት ነው የሚባለው፡፡
ተስፋ ገና ሳለች ልጅህን ገሥጽ፥ መሞቱንም አትሻ። ምሳሌ 19፡18
አባት ልጅ መውለዱን ልጅን ወደዚህ ለማምጣት ምክኒያት መሆኑን ብቻ ካየና ወደዚህ አለም ያመጣውን ልጁን ኮትኩቶና አርሞ የማሳደግ ሃላፊነት የማይወስድ ከሆነና ለራሱ ብቻ የሚኖር ራስ ወዳድ ከሆነ ልጁ በኣባትነት እንክብካቤ እጦት ይሰቃያል፡፡ በዚያም ምክኒያት ልጁ ሃላፊነትን ሊወስድ የሚችል በተራው ልጅን ወልዶ በስርአት የሚያሳድግ ዜጋ መሆን ይሳነዋል፡፡
መፅሃፍ ቅዱስ በቤተክርስቲያን መሪነት ሃላፊነት ስለሚሰጠው መሪ መመዘኛ ሲናገር እንዲህ ይላል፡፡
ልጆቹን በጭምትነት ሁሉ እየገዛ የራሱን ቤት በመልካም የሚያስተዳድር፤ 1ኛ ጢሞቴዎስ 3፡4
ስለዚህ ራስ ወዳድ ያልሆኑ ፡ ልጆቻቸውን ሳያስቆጡዋቸው በትግስትና በትጋት የሚመክሩና የሚያደሳድጉ ለቤተሰብ መታነፅ በትጋር የሚሰሩ አባቶች ያስፈልጉናል፡፡ አዎን ለልጆቻቸው እግዚአብሄርን ስለመፍትራትና በቃሉ ስለመኖር መልካም ምሳሌ የሚሆኑ አባቶች ያስፈልጉናል፡፡
እናንተም አባቶች ሆይ፥ ልጆቻችሁን በጌታ ምክርና በተግሣጽ አሳድጉአቸው እንጂ አታስቆጡአቸው። ኤፌሶን 6፡4
አባት ለገዛ ቤተሰዎቹ ብቻ ሳይሆን በተለያየ ምክኒያት የአባነት እንክብካቤ ለማያገኙ ሌሎች ልጆች በቻለው መጠን ይብዛም ይነስም በህይወታቸው የአባትነትን ሚና መጫወት ይገባዋል፡፡
በተለይም ደግሞ በስጋ ያልወለዱዋቸውን ልጆች በማደጎ በማሳደግ ስጋዊም ሆነ መንፈሳዊ የአባትነትን ሃላፊነት የሚወስዱና በዚህ የሚያገለግሉ ሰዎች ክብር ሊሰጣቸው ይገባል፡፡

Thursday, June 16, 2016

የክርስትናችን ማተብ

ክርስትና የህይወት ጉዳይ ነው፡፡ ክርስትና ለሞተልን ለእየሱስ እና ለእርሱ ብቻ መኖር ነው፡፡ ታዲያ የአማኝ ክርስቲያን ምልክቱ ምንድነው? ክርስቲያን ክርስቲያንነቱ በምን ይታወቃል? አንድን ክርስቲያን በስም ብቻ ሳይሆን በእውነት ክርስቲያን የሚያደርገው ምንድነው?

ይህ ጥያቄ በህይወታችን ቸል ልንለው የማይገባ ነገር ግን በሚገባ ከልባችን ልንመልሰው የሚገባን ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡ ይህን ወሳኝ ጥያቄ በሚገባ መመለሳችን ህይወታችንን በከንቱ እንዳንሮጥ ይጠብቀናል፡፡

የአማኝነት ምልክት ምንድነው? የክርስቲያንነታችን እውነተኛ መለያ ምንድነው?

እንግዲህ ሁልጊዜ ታምነን፥ በእምነት እንጂ በማየት አንመላለስምና በሥጋ ስናድር ከጌታ ተለይተን በስደት እንዳለን የምናውቅ ከሆንን፥ ታምነናል 2 ቆሮንቶስ 55-8

የክርስትናችን ምልክት እምነታችን ነው፡፡ ክርስትናችን በልብሳችን ክርስትናችን አንገታችን ላይ በምናደርገው ምልክት ምልክት አይታወቅም፡፡
የክርስትና እምነታችን ደግሞ የሚታየው በአኗኗራችን ነው፡፡ የአማኝ ክርስቲያን ምልክቱ ለጊዜው በምድር ላይ ሲኖር ወደ መንግስተ ሰማያት እሰከሚሄድ ድረስ ከጌታ እየሱስ ተለይቶ በስደተኝነት እንደሚኖር ማወቁ ነው፡፡ የአማኝ ምልክቱ የስደተኛ ኑሮ ነው፡፡

ሰው ግን በምድር ላይ ሲኖር የሚፈራው አምላክ እንደሌለው እንደ ልቡ በራሱ ላይ ራሱ ጌታ ሆኖ በራሱ መንገድ የሚኖር ከሆነ የአማኝነት ማተብ የለውም፡፡

ሰው ግን በምድር ላይ ሲኖር ዛሬ ነገ እንሞታለንና እንብላና እንጠጣ (1 ቆሮንቶስ 1532) በሚል አስተሳሰብ የሚኖር ከሆነ አማኝ አይደለም፡፡

ሰው ግን በምድር ሲሆን እንደ እንግዳና መጻተኛ የማይኖርና በአለም ክፉ ውድድር ውስጥ ገብቶ በአለም ስጋዊ ምኞት የሚኖር ከሆነ አልታመነም፡፡
ወዳጆች ሆይ፥ ነፍስን ከሚዋጋ ሥጋዊ ምኞት ትርቁ ዘንድ እንግዶችና መጻተኞች እንደ መሆናችሁ እለምናችኋለሁ፤ 1 ጴጥሮስ 211

ሰው ግን በምድር ሲኖር ምድር ጊዜያዊ ብቻ መኖሪያው እንደሆነ ወደ መንግስተ ሰማያት እንደሚሄድ በእግዚአብሄር ፊት እንደሚቀርብና እንደሚጠየቅ አድርጎ እግዚአብሄርን በመፍራት ካልኖረ የክርስትና ማተብ የለውም፡፡

መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው። እኛ አገራችን በሰማይ ነውና፥ ከዚያም ደግሞ የሚመጣ መድኃኒትን እርሱንም ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን እንጠባበቃለን፤ ፊልጵስዩስ 319-20

መፅሃፍ ቅዱስ በእምነታቸው ስለተመሰከረላቸው ስለእምነት አባቶች ሲናገር በዕብራዊያን መፅሃፍ ላይ እንዲህ ይለናል፡፡
እነዚህ ሁሉ አምነው ሞቱ፥ የተሰጣቸውን የተስፋ ቃል አላገኙምና፤ ዳሩ ግን ከሩቅ ሆነው አዩትና ተሳለሙት፥ በምድሪቱም እንግዶችና መጻተኞች እንዲሆኑ ታመኑ ዕብራውያን 1113